Tender Detail

Tender Details

  • Company Yiha Real Estate P.L.C (ይሓ ሪል እስቴት ኃላ/የተ/የግ/ማህበር)
  • Address አዲስ አበባ ስቴድየም ቤተ ዛታ ሆስፒታል ፊት ለፊት "ይሓ ሲቲ ሴንተር" ህንጻ 2ኛ ፎቅ, Phone: 011-5-58-01-29
  • Website
  • Deadline21 Oct 2024, 10:00 AM
  • magazine
  • Bid Document Price
  • opening date
  • Categories

ይሓ ሪል እስቴት ኃላ/የተ/የግ/ማህበር ከዚህ ቀጥሎ የተዘረዘሩት እቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡


የግዢ ጨረታ ማስታወቂያ

ይሓ ሪል እስቴት ኃላ/የተ/የግ/ማህበር ከዚህ ቀጥሎ የተዘረዘሩት እቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

    1. የጽህፈት መሳሪያ እቃዎች /እስክርቢቶ ሰማያዊ፣ ጥቁር፣ ፕሪንተር፣ ቶነር ወዘተ ዝርዝሩንና ብዛቱን በጨረታ ሰነዱ ላይ ተጠቀሷል፡፡
    2. የፅዳት እቃዎች/ የልብስ ሳሙና፣ የገላ ሳሙና፣ ፈሳሽ ሳሙና፣ ሶፍት፣ በረኪና፣ ዲቶል ወዘተ ዝርዝሩንና ብዛቱን በጨረታ ሰነዱ ላይ ተጠቅሷል፡፡

በዚህ መሰረት፡-

  1. ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 400 /አራት መቶ ብር/ በመክፈል ከፋይናንስ ከፍል መግዛት ይችላሉ፡፡
  2. የተጫራቾች የታደሰ ንግድ ፈቃድ፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥርና የቫት መመዝገቢያ ሰርተፊኬት ኮፒ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  3. የጨረታ ማስከበሪያ በጨረታ ሰነዱ ላይ የተገለፀው የብር መጠን በባንክ በተመሰከረበት (CPO) ብቻ ማስያዝ ይኖርበታል፡፡
  4. ተጫራቾች የእያንዳንዱ ዕቃዎች ብራንዳቸውንና ሌሎች የዕቃው መገለጫዎች በጨረታ ሰነዱ መሰረት መገለጽ ይኖርበታል፡፡
  5. ተጫራቾች ለመወዳደር በመረጡት ለእያንዳንዱ ዕቃ ናሙና ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
  6. በጨረታው መሰረት ተጫራቹ አሸናፊ የሆነባቸውን ዕቃዎች አሸናፊ መሆኑን ከተነገረበት ቀን ጀምሮ በሶስት የሥራ ቀናት ጊዜ ውስጥ በራሱ መጓጓዣ ስቴድየም ወደ ሚገኘው ይሓ ሲቲ ሴንተር ህንጻ የይሓ ሪል እስቴት ንብረት ከፍል /11 ፎቅ ድረስ በማጓጓዝ ማስረከብ ይኖርበታል፡፡
  7. ለአሸናፊው ድርጅት/ ግለሰብ የዕቃዎቹን ዋጋ የሚከፈለው ዕቃዎቹን ሙሉ በሙሉ ካስረከበ በኋላ ይሆናል።
  8. የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 7 /ሰባት/ ተከታታይ የስራ ቀናት ከድርጅቱ መግዛት ይችላሉ፡፡
  9. ጨረታው የሚዘጋበት ቀንና ሰዓት የጨረታው ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 8 /ስምንተኛው የሥራ ቀን በስራ ሰዓት ከጠዋቱ 400 ሰዓት ይሆናል፡፡
  10. ጨረታው የሚከፈትበት ቀንና ሰዓት ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ 8 /ስምንተኛው የሥራ ቀን በስራ ሰዓት ከጠዋቱ 430 ሰዓት ይሆናል፡፡
  11. ጨረታው በሚከፈትበት ጊዜ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው መገኘት ይችላሉ፡፡

አድራሻ - አዲስ አበባ ስቴድየም ቤተ ዛታ ሆስፒታል ፊት ለፊት "ይሓ ሲቲ ሴንተር" ህንጻ 2 ፎቅ

ስልክ ቁጥር የቢሮ ፡-  011-5-58-01-29/12/03

ሞባይል፡- 09-22-07-95-75/09-11-41-79-04

ማሳሰቢያ፡- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::

 

ይሓ ሪል እስቴት ኃላ/የተ/የግ/ማህበር

Save Tender