በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የአዳሚ ቱሉ የፀረ ተባይ ማዘጋጃ ፋብሪካ ከዚህ በታች ከሎት 1-5 የተገለጹ ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር APPF/04/17
- በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የአዳሚ ቱሉ የፀረ ተባይ ማዘጋጃ ፋብሪካ ከዚህ በታች ከሎት 1-5 የተገለጹ ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
- ሎት 1 ለሰራተኞች አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ አልባሳት እና ጫማዎችን
- ሎት 2 የተለያዩ የፅህፈት መሳሪያዎች እና የተለያዩ የፅዳት እቃዎች
- ሎት 3 የተለያዩ የተሽከርካሪዎች ጎማዎች
- ሎት 4 የተለያዩ የሰራተኞች የሥራ የአደጋ ደህንነት መከላከያ ዕቃዎች (personal protective safety equipment) ብዛት የተለያየ እና
-
- ሎት 5 የተለያዩ የIT እቃዎች ግዥ መግዛት ይፈልጋል።
- ተጫራቾች የዘመኑን ግብር የከፈሉበት የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸው መሆን ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች በመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ የተመዘገቡበት የምስከር ወረቀትና ከገቢዎችና ጉሙሩክ ሚኒስቴር በጨረታ እንዲሳተፉ የተጻፈላቸው የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች አዳሚ ቱሉ ባለው የፋብሪካው ዋና መስሪያ ቤት ወይም አዲስ አበባ ቦሌ ሩዋንዳ ከኩዌት ኤምባሲ 10 ሜትር ገባ ብሎ ጅቡቲ ኤምባሲ ፊትለፊት ከሚገኘው ማስተባበሪያ ቢሮ የማይመለስ ብር አምስት መቶ ብቻ (500.00) በመክፈል የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የሚያቀርቡት የጨረታ ሰነድ ላይ የተጫራቹ ድርጅት ስምና አድራሻ በትክከል ተፅፎ የድርጅቱ ማህተም ያረፈበት መሆን ይኖርበታል፡፡ ተጫራቶች ቴክኒካል እና ፋይናንሺያል ሰነዶቻቸውን ኮፒ እና ኦሪጅናሉን በተለያየ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ለሚጫረቱበት እቃ በራሳቸው የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ በመሙላት በተጫራቹ ድርጅት ኃላፊ ተፈርሞና ማህተም በማድረግ ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች ለጨረታ ያቀረቡትን ጠቅላላ ዋጋ 2% የጨረታ ማስከበሪያ በአዳሚ ቱሉ የፀረ-ተባይ ማዘጋጃ ፋብሪካ ስም የባንከ የክፍያ ትዕዛዝ (CPO) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ከጨረታው የቴክኒካል ሰነድ ጋር ለብቻው በፖስታ በማሸግ ማቅረብ አለባቸው::
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን እስከ ህዳር 24 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 በፊት የፋብሪካው ዋና መስሪያ ቤት ወይም አዲስ አበባ ማስተባበሪያ ቢሮ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ የጨረታ መከፈቻው እለት ህዳር 24 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአዲስ አበባ ማስተባበሪያ ቢሮ ይሆናል፡፡
- ፋብሪካው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር፡- አ/ቱሉ 0464419164 (ማዞሪያ) ፣ 0991625748 (ግዥ ቡድን) 0991589980 (ንግድ መምሪያ) ፖ.ሣ.ቁ 247 (አ/ቱሉ) አ.አ ማስተባበሪያ ስልክ ቁጥር 011 662 4656 ፖ.ሣ.ቁ 1206 (አ.አ)
በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የአዳሚ
ቱሉ የፀረ-ተባይ ማዘጋጃ ፋብሪካ
