የኢትዮጵያ ፖስታ ለ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት ከዚህ በታች ለተዘረዘሩት የግዥ አይነቶች ሎት (Lot) መሠረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ግጨ/09/2017 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ፖስታ ለ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት ከዚህ በታች ለተዘረዘሩት የግዥ አይነቶች ሎት (Lot) መሠረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም :- በጨረታው ለመካፈል የሚፈልጉ ተጫራቾች ከታች በተገለፁት የጨረታ አይነቶች በድርጅቱ ገንዘብ ቤት 2ኛ ፎቅ የማይመለስ ብር 300.00 /ሶስት መቶ ብር/ በየሎቱ በመክፈልና ግዥ ክፍል በመቅረብ የጨረታ ሰነዱን በመውሰድ የእያንዳንዱን ሎት ከጨረታ ሰነዱ ጋር በተያያዘው እስፔስፊኬሽን መሠረት ዋጋ በመሙላት ኦርጅናልና ፋይናንሻል ዶክመንት በተናጠል CPO ከኦርጅናል ቴክኒካል ዶክመንት ጋር በማያያዝ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ከታች በሠንጠረዥ 1 በተቀመጠው ሎት ዝርዝር እና ቀነ ገደብ እንዲሁም የጨረታ መዝጊያ ቀን መሠረት ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ እስከ 6:30 ሰዓት ድረስ ሠነዱን ከገዙበት ግዥ ከፍል 2ኛ ፎቅ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
ተጫራቾች በቅድሚያ ተመላሽ የሚሆን የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ CPO ከዚህ በታች በተዘረዘሩ መሠረት ለምትጫረቱበት ግዥ አይነት በየሎቱ ማለትም፡-
- ከሎት 1-5 ለየቱ 50,000.00 /ሃምሳ ሺህ ብር/ CPO ሲፒዮ እንዲሁም ከሚያቀርቡት የጨረታ ሰነድ ጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ የጨረታው ኤንቨሎፕ ህዳር 25 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድርጅቱ ሠራተኞች ከበብ ይከፈታል፡፡ በተጨማሪም በየሎት አይነታቸው ዋጋ በመሙላት የሚቀርብ ሆኖ ለእያንዳንዱ ሎት ዋጋ የሚሰጠው በተናጠል መሆኑን እንገልጻለን፡፡
ሠንጠረዥ 1 የጨረታ ሰነድ መመለሻና መክፈቻ ሰዓትና ቀን መግለጫ
|
ተራ ቁ. |
ሎት |
የጨረታ አይነቶች |
ሰነዱ የሚመለስበት የመጨረሻው ቀን እና የመክፈቻ ሰዓት |
|
1 |
ሎት 1 |
ዲጂታል ሚዛን |
|
|
2 |
ሎት 2 |
የመልዕክት መላኪያ ሸራ |
|
|
3 |
ሎት 3 |
የማስታወቂያ ኤጀንሲ ቅጥር |
|
|
4 |
ሎት 4 |
ቀይ እና ቢጫ ታግ |
|
|
5 |
ሎት 5 |
የመልዕከት መላኪያ ካርቶን ማሸግ ሥራ |
ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ሲፒዮ ሲያሰሩ ለፖስታ አገልግሎት ድርጅት / Ethioplan Postal Service enterprise በሚል ያሰሩ
የኢትዮጵያ ፖስታ
