የኮ/ቀ/ክ/ከ/ፖ/መምሪያ በ2017 ዓ/ም በጀት ዓመት ለመምሪያው እና በስሩ ለሚገኙት ፖሊስ ጣቢያዎች የሚውል ከዚህ በታች በሎት የተገለፁ በጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 002/2017 ዓ/ም
የኮ/ቀ/ክ/ከ/ፖ/መምሪያ በ2017 ዓ/ም በጀት ዓመት ለመምሪያው እና በስሩ ለሚገኙት ፖሊስ ጣቢያዎች የሚውል ከዚህ በታች በሎት የተገለፁ በጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፡፡
ሎት 1 የፅህፈት መሳሪያዎች፣
ሎት 2 የፅዳት ዕቃዎች፣
ሎት 3 የህትመት ውጤቶች
ሎት 4 የፅዳት ሠራተኞች አልባሳት
ሎት 5 የዳቦ የሚሆን ዱቄት
ሎት 6 የመሬት ምንጣፍ ማፅጃ ማሽን እና የመድሃኒት ማስቀመጫ ፍሪጅ
ስለዚህ በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች -
- የዘመኑን ግብር የከፈሉበት ማስረጃ እና በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያለው፣
- የግብር ከፋይነት ምዘገባ ምስከር ወረቀት ያለው፣
- የቫት ተመዝጋቢ የሆኑና የምዝገባ ሰርተፍኬት ያለው፣
- የአቅራቢነት ምዝገባ የምስክር ወርቀት ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች 1-4 የተጠቀሱትን የንግድ ፍቃድ፣ የቫት የቲን መለያ ቁጥር እና የአቅራቢነት ምዘገባ መረጃዎችን የጨረታ ዶክመንት ሲገዙ ኦርጅናሉንና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ አቅርበው እንዲመሳከር የማድረግ ግዴታ አለባቸው፣ በመሆኑም ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 10 የስራ ቀናት ኮ/ቀ/ከ/ከ/ፖ/መምሪያ /ግዥ/አስ/ር ዲቪዚዮን 4ኛ ፎቅ የጨረታው ሰነድ የማይመለስ ብር 300 /ሶስት መቶ ብር/ ብቻ በመከፈል መግዛት ይቻላል፤ .
- ተጫራቾች በሚጫረቱበት የዕቃ መጠን 1.5% ለእያንዳንዱ ሎት1 ብር 5000፤ ሎት2 ብር 3000፣ ሎት3 ብር 4000፣ ሎት4 ብር 3000፣ ሎት5 ብር 10,000 እና ሎት 6 ብር 8000 ሲሆን ከአንድ ሎት በላይ የሚጫረቱት ተጫራቾች የሎቶቹ ድምር የጨረታ ማስከበሪያ በባንከ በተረጋገጠለት ሲ.ፒ.ኦ በኮ/ቀ/ክ/ከ/ፖ/መምሪያ ስም አዘጋጅቶ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል ፤
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበት ሰነድ ቴክኒካል እና ፋይናንሻል በተለያዩ ፖስታ በማስገባት ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ እስከ 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ዘወትር በስራ ሰዓት ኮ/ቀ/ከ/ክ/ፖ/መምሪያ ፋ/ግዥ/ዲቪዚዮን 4ኛ ፎቅ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ በማስገባት አለባቸው::
- የጨረታ ሳጥን በ11ኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ኮ/ቀ/ክ/ከ/ፖ/መምሪያ ፋ/ግዥ/ዲቪዚዮን 4ኛ ፎቅ ከጠዋቱ 4:30 ሰዓት ይከፈታል።
- አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፈባቸውን ዕቃዎች በራሳቸው ትራንስፖርት ግዥ ፈፃሚው መስሪያ ቤት ድረስ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን ዕቃዎች ለእያንዳንዱ ከቫት ጋር ያለውን ዋጋ ማስቀመጥ ይጠበቅባችኋል።
- በተሰጠው የጨረታ ሰነድ ብቻ ሞልቶ ማቅረብ ይገባዋል፡፡
- ሎት 1፣2፣4 እና 5 ተጫራቾች ናሙና ማቅረብ አለባቸው፣ ሎት 3 መስሪያ ቤቱ ናሙና ያቀባል።
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበት ሎት (ዕቃዎች) አማራጭ ዋጋ ማስቀመጥ አይቻልም፡፡
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ አድራሻ ፡- ኮልፌ ቀራኒዮ ከፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ከጦርሃይሎች በስተቀኝ ቀለበት መንገድ ሲወርዱ የቀድሞው ቶታል 3 ቁጥር ማዞሪያ ሳይደርሱ ኦሜጋ ትምህርት ቤት አጠገብ
ስልክ ቁጥር ፡- 011-3-20-44-46/011-371-77-41 ደውለው መረዳት ይችላሉ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ኮሚሽን የኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከ
ፖሊስ መምሪያ
