በአርሲ ዞን ማረሚያ ቤት ውስጥ ለሚገኙት የሕግ ታራሚዎች የበሰለ ምግብ ወይም ለምግብ አቅርቦት የሚውል ጥሬ እህል እና የተለያዩ ማጣፈጫዎችን እንዲሁም የማገዶ እንጨት የ2017 ዓ.ም በጀት ከጥር 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 30/2017 ዓ.ም ለ6/ስድስት/ ወር ለሚቆይ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
በአርሲ ዞን ማረሚያ ቤት ውስጥ ለሚገኙት የሕግ ታራሚዎች የበሰለ ምግብ ወይም ለምግብ አቅርቦት የሚውል ጥሬ እህል እና የተለያዩ ማጣፈጫዎችን እንዲሁም የማገዶ እንጨት የ2017 ዓ.ም በጀት ከጥር 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 30/2017 ዓ.ም ለ6/ስድስት/ ወር ለሚቆይ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ በዚህ መሠረት ማንኛውም ጨረታውን ለመካፈል የሚፈልግ ድርጅት ወይም ግለሰብ
- ተወዳዳሪዎች የገንዘብ እና የኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር ወይም ቢሮ ወስጥ የተመዘገቡና የዘመኑን የሥራ ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ እና አግባብነት ያለው የ2017 የታደሰ የንግድ ሥራ ፍቃድ ያላቸው መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) የተመዘገቡ ወይም የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ የሚያቀርቡ መሆን አለባቸው፡፡
- የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 500 /አምስት መቶ/ ከፍሎ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት ከዞን ማረሚያ ቤት አስተዳደር ጽ/ቤት በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የዋጋ ማቅረቢያ ሰነዳቸውን በሰም በታሸገ ፖስታ በማድረግ በማረሚያ ቤት አስተዳደር ጽ/ቤት ውስጥ ለዚህ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ በማስገባት መወዳደር አለባቸው፡፡
- ተጫራቾቹ የጨረታ ማስከበሪያ ከመቶ 2% በጥሬ ገንዘብ ወይም በተመሰከረለት ቼክ እና የምግብ እህል ናሙና ከጨረታ ሰነድ ጋር አያይዞ ማቅረብ አለባቸው፡፡
- በጥቃቅን እና አነስተኛ ተደራጅቶ የበሰለ ምግብ ለማቅረብ የሚቀርቡ ማህበራት ቅድሚያ ይሰጣቸዋል፡፡ ይህ ካልተገኘ በጥሬ እህል እናወዳድራለን፡፡
- ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀን በአየርላይ ውሎ በ16ኛው ቀን በሥራ ቀን ከረፋዱ በ4፡00 ሰዓት በዞን ማረሚያ ቤት አስተዳደር ጽ/ቤት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው እንዲሁም የሕግ ታራሚ ኮሜቴዎች እና የማረሚያ ቤቱ ጨረታ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- የዞኑ ማረሚያ ቤት አስተዳደር ጽ/ቤት የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- በጥቃቅንና አነስተኛ ተደራጅቶ የበሰለ ምግብ ለማቅረብ የሚቀርቡ ማህበራት በማረሚያ ቤቱ ውስጥ በተዘጋጀ ማብሰያ ቤት ውስጥ በተዘጋጀ ማብሰያ ቤት ውስጥ ምግብ አብስሎ ማቅረብ የሚችል፡፡
- ማረሚያ ቤቱ የሚገኝበት ከተማ በአርሲ ዞን አሰላ ማረሚያ ቤት
ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0223311040/0913439972
በኦሮሚያ ማረሚያ በቤቶች አስተዳደር ኮሚሽን አርሲ ዞን ማረሚያ ቤት
አሰላ
