የኦሮሚያ ኢንዱስትሪያል ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ያለውን ERP ማሰራት ይፈልጋል። ኮርፖሬሽኑ ከዚህ በታች ያሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተወዳዳሪዎችን በኮርፖሬሽኑ ጽ/ቤት በመገኘት የጨረታ ሠነድ እና የቴክኒከ መገምገሚያ ሰነድ በግዥ በመውሰድ መወዳደር የሚችሉ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡
ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
ENTERPRISE RESOURCE PLANNING (ERP)
REQUEST FOR EXPRESSIONS OF INTEREST
(CONSULTING SERVICES-FIRMS SELECTION)
የኦሮሚያ ኢንዱስትሪያል ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ያለውን ERP ማሰራት ይፈልጋል። ኮርፖሬሽኑ ከዚህ በታች ያሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተወዳዳሪዎችን በኮርፖሬሽኑ ጽ/ቤት በመገኘት የጨረታ ሠነድ እና የቴክኒከ መገምገሚያ ሰነድ በግዥ በመውሰድ መወዳደር የሚችሉ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡
በመሆኑም ተወዳዳሪዎች ፡-
- ከሚመለከተው አካል የሙያ ብቃት ማረጋገጫ የወሰዱና በዘመኑ ያሳደሱ፤
- የዘመኑን ግብር የከፈሉና የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ እንዲሁም በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል የምዝገባ ምስከር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፤
- ከዚህ በፊት ተመሳሳይ ድርጅቶች ERP ሥራ ስለመሥራታቸው የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤
- የጨረታው ተወዳዳሪዎች በጨረታው ለመወዳደር የሚያስችላቸው መስፈርቶችን ማለትም፦
ሀ/ ድርጅቱ በሥራ ላይ የቆየበትን የሥራ ዘመንና ያላቸውን ሙያተኛ ብዛት፤
ለ/ በሥራ ላይ የሚያሠማሩትን ሙያተኞች ብዛት፤ የትምህርት ደረጃቸውን እና የሥራ ልምዳቸውን (Work Experiences)
ሐ/ ውል ከተፈረመበት ቀን ጀምሮ በምን ያህል ቀናት ውስጥ ሥራውን እንደሚጀምር፤
መ/ ሥራውን በሚያጠናቅቅበት ጊዜ ብዛት እንዲሁም፤
ሠ/ የሚሠሩበትን ጠቅላላ ዋጋ ተ.ኦ.ታ (VAT) ጨምሮ መግለጽ ይኖርበታል፤
- የፕሮፖዛል ሠነዱን ዋና እና ኮፒ ፋይናንስ እና ቴክኒካል ለየብቻ የታሸገ መሆን አለበት፣
- የጨረታው ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ በተረጋገጠ ቼክ (CPO) 1 (CPO) ብር 50,000 (ሃምሳ ሺህ ብር) ማስያዝ የሚችሉ፤
- ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን አንስቶ ክፍት ሆኖ ለ15 ሥራ ቀናት ከቆየ በኋላ በ16ኛው ቀን 8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን 8፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ተወካዮች ባሉበት ይከፈታል። ተጫራቾች አለመገኘት የጨረታውን መከፈትን አያስተጓጉልም። 16ኛ ቀን በሥራ ቀን ካልዋለ በሚቀጥለው በ17ኛ የሥራ ቀን ይሆናል።
- ኮርፖሬሽኑ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ ፡- +251913812486 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
አድራሻ ፡- ሜክሲኮ፣ ከሱዳን ኤምባሲ አጠገብ በስተምስራቅ በኩል፣ አ.አ፣ ኢትዮጵያ (Mexico, Next to the Republic of Sudan Embassy in East Direction Addis Ababa. /Finfinnee/. Ethiopia)
የኦሮሚያ ኢንዱስትሪያል ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን
