የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓት ልማት ድርጅት (ኢኢግልድ) ሎት 1 የደንብ ልብስ አቅርቦት እና ሎት 2 የሞባይል ስልክ ቀፎ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓት ልማት ድርጅት (ኢኢግልድ)
ሎት 1 የደንብ ልብስ አቅርቦት እና
ሎት 2 የሞባይል ስልክ ቀፎ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፡፡
ማንኛውም ተጫራች በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታከስና የግብር ከፋይነት ምዝገባ ሰርተፍኬት፣ በመንግስት ግዢና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዝርዝር የተመዘገበበት የምስክር ወረቀትና ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን በጨረታ እንዲሳተፍ የተፃፈለትን የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችል መሆን ይኖርበታል፡፡ ለዚህ የተዘጋጀውን ዝርዝር የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ) በመክፈል ከድርጅቱ የግዥ ቡድን በመቅረብ መውሰድ ይችላሉ፡፡
ተጫራቶች ቴክኒካልና ፋይናንሻል ሰነዶች ኦርጂናልና ኮፒ በተለያዩ በታሸጉ ፖስታዎች በማድረግ እንዲያቀርቡ እያሳሰብን ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት በአየር ላይ ቆይቶ በማግስቱ በ16ኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኢኢግልድ ዋና መ/ቤት ስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል፡፡ ነገር ግን 16ኛው ቀን በዓል ከሆነ ቀጥሎ ባለው የስራ ቀን ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች ለሚወዳደሩባቸው የደንብ ልብስ ናሙና (ሳምፕል) ከጨረታው ሰነድ ጋር ማቅረብ አለባቸው፡፡
ተጫራቾች በጨረታ ለመወዳደር የጨረታ ማስከበሪያ ለሎት 1 ብር 100,000 (አንድ መቶ ሺ) እና ለሎት 2 ብር 25,000.00 (ሃያ አምስት ሺ) በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት (Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise) ስም በሲ.ፒ.ኦ. ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ከጨረታው ቴክኒካል ሰነድ ጋር በማያያዝ ማቅረብ አለባቸው፡፡
በጨረታ መክፈቻ ሰዓት የተጫራቾች አለመገኘት ጨረታውን አያስተጓጉለውም ፡፡
ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ ፡- አዲስ አበባ በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 ፒያሳ ከሊፋ ህንፃ አካባቢ በስተሰሜን አቅጣጫ የባቡር ሃዲዱን ተሻግሮ ወደ ዮሃንስ በሚወስደው መንገድ ጣሊያን ሰፈር (የቀድሞ ጅንአድ መ/ቤት)።
ተጨማሪ ማብራሪያ ቢያስፈልግ ፡- በስልክ ቁጥር 011-1-57-24-97/ በመደወል ወይም በአካል በመገኘት መጠየቅ ይችላሉ
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት
