በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የሶዶ መንገድ ጥገና ዲስትሪከት የተለያየ መጠን ያላቸውን ብረታ ብረቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የውስን ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ኢመአ ሶዶ ዲስትሪክት 03/2017 ዓ.ም
በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የሶዶ መንገድ ጥገና ዲስትሪከት የተለያየ መጠን ያላቸውን ብረታ ብረቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ በዚህም መሠረት በመንግስት የግዢና ንብረት አስተዳደር መመሪያ መሠረት ህጋዊ ፈቃድ ያላቸው ብቁ ተጫራቾችን በጨረታው እንዲሳተፉ ይጋበዛል፡፡
- ማንኛውም በዘርፉ የተሰማራ የዘመኑን ግብር የተከፈለበት የንግድ ፈቃድ የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያለው በጨረታው መሳተፍ ይችላል፡፡
- ተጫራቶች የመንግስት ድርጅቶች በሚያወጡት ጨረታ ላይ ለመሳተፍ እንዲችሉ በግዥ ኤጀንሲ ዌብሳይት ላይ የተመዘገቡ መሆኑን ማረጋገጫ ማቅረብ አለባቸው::
- ተጫራቾች ዝርዝር መግለጫ የያዘውን የጨረታ ሰነድ ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን አንስቶ በተከታታይ 15 ቀናት ውስጥ በሥራ ሰዓት በመ/ቤታችን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000322276919 የማይመለስ ብር 300.00 (ሶስት መቶ ብር) ገቢ በማድረግ ዘወትር በሥራ ሰዓት ወላይታ ሶዶ ከነዳጅ ዲፖ አለፍ ብሎ ጎፋ ማዞሪያ አካባቢ ባለው ቢሮ በመምጣት ዝርዝር መረጃ የያዘ የጨረታ ሠነድ መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ የሚያቀርቡት የገንዘብ መጠን 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) በባንክ በተረጋገጠ (CPO) ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (Bid Bond) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን በታሸገ ኤንቨሎፕ የጨረታ ቁጥሩን በመግለፅ ለተከታታይ 15 ቀናት በስራ ሰዓት ከሰኞ-ዓርብ ከመታሸጉ በፊት በተጠቀሰው አድራሻ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
- ጨረታው ከላይ በተጠቀሰው መሰረት በዚሁ ዕለት ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ታሽጐ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ተጨማሪ ማብራሪያ ቢያስፈልግዎ በስልክ ቁጥር 046-551-12-92 መደወል ይችላሉ፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ፡- ስልክ ቁጥር 046-5511292 ፖስታ ሳጥን ቁጥር 116
አድራሻ፡- ወላይታ ሶዶ ከነዳጅ ዲፖ አለፍ ብሎ ጎፋ ማዞሪያ
በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
የሶዶ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት
