አልፎራ አግሮ ኢንዱስትሪ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር በስሩ ለሚገኝ ለመልጌ ወንዶ እና ኮምቦልቻ የምግብ ማቀነባበሪያ ጥብዓት የሚሆን የአኩሪ አተር ዘይት ወይም የሱፍ ዘይት በባለ አምስት (5) ሊትር ጠቅላላ ብዛቱ 396,000.00 ሊትር ግዥ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር EL/LP-04/2024
አልፎራ አግሮ ኢንዱስትሪ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር በስሩ ለሚገኝ ለመልጌ ወንዶ እና ኮምቦልቻ የምግብ ማቀነባበሪያ ግብዓት የሚሆን የአኩሪ አተር ዘይት ወይም የሱፍ ዘይት በባለ አምስት (5) ሊትር ጠቅላላ ብዛቱ 396,000.00 ሊትር ግዥ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
- አምራች አከፋፋይ ወይም አስመጪ መሆናቸውን የሚገልጽ መረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
- ተጫራቾች አግባብነት ያለው የንግድ ፈቃድ ያላቸው መሆን አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው።
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ የሚያስችላቸውን የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሚመለስ ብር 500,000 (አምስት መቶ ሺህ) በሲፒኦ ወይም በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ ባንክ ጋራንቲ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ጨረታውን ያሸነፈው ድርጅት ለመልካም ስራ አፈጻጸም ዋስትና ጠቅላላ ካሸነፈው አቅርቦት ክፍያ ብር ላይ 10% በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይኖርበታል፡፡
- ተጫራቾች በዋጋ ማቅረቢያ ሰነዱ ላይ በተዘረዘረው እና በተያያዘው የአቅርቦትና የጥራት መሥፈርት መሠረት ጨረታውን መጫረት ይችላሉ።
- ተጫራቾች ይህ ጨረታ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከሰኞ እስከ አርብ ዘወትር በስራ ሰአት ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት እስከ ቀኑ 11፡00 ሰዓት እንዲሁም ቅዳሜ እስከ ቀኑ 6፡00 ሰዓት የጨረታ ሰነዱን አዲስ አበባ ላም በረት አካባቢ ከሚገኘው የድርጅቱ አቅርቦት መምሪያ ክፍል ዘወትር በስራ ሠዓት በመምጣት የማይመለስ 200.00 ብር በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ሰነዳቸውን እስከ ታኅሣሥ 18 ቀን 2017 ዓ.ም እስከ ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ቀን ከጠዋቱ 4:30 ላምበረት በሚገኘው የኤልፎራ ህንጻ 8ኛ ፎቅ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታው ይካሄዳል፡፡
- ኩባንያው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር +251 116461076/+251 976806076/092771869 በመደወል መጠየቅ ይችላሉ፡፡
ኤልፎራ አግሮ ኢንዱስትሪ ኃ/የተ/የግ/ማህበር
