የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከየካ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ በተፃፈልን ደብዳቤ መሠረት የፌዴሬሹኑ ህንፃ በሚገኝበት አካባቢ ከወንጀል ለመከላከል ይረዳ ዘንድ የውጪ የደህንነት ካሜራ መግጠም ስለፈለገ በቀረበው Spacification መሠረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከየካ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ በተፃፈልን ደብዳቤ መሠረት የፌዴሬሹኑ ህንፃ በሚገኝበት አካባቢ ከወንጀል ለመከላከል ይረዳ ዘንድ የውጪ የደህንነት ካሜራ መግጠም ስለፈለገ በቀረበው Spacification መሠረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በዚሁ መሠረት ፡-
- በጨረታው ለመወዳደር የምትፈልጉ ተጫራቾች የታደስ ንግድ ፍቃድ ያላቸው፣ የቲን እና ቫት ተመዝጋቢ የሆኑ::
- ተጫራቾች የጨረታውን ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ከጨረታ ሰነድ ጋር የሚያቀርቡትን ዕቃ የጠቅላላ ዋጋውን ቫትን ጨምሮ 2% አያይዘው ማቅረብ አለባቸው::
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዶቻቸውን ዋናውንና ኮፒውን በታሸገ ኤንቨሎፕ ማስታወቂያ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ለተከታታይ 10 የሥራ ቀናት በፌዴሬሽኑ ቢሮ ቁጥር 5 ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል::
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአስረኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚያው ዕለት 4፡30 ሰዓት በፌዴሬሽኑ ቢሮ ቁጥር 5 (መሰብሰቢያ አዳራሽ) ይከፈታል::
- ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን ዕቃዎች ከቫት ጋር ያለውን ዋጋ ማስቀመጥ ይጠበቅባቸዋል::
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ሰነድ ከቢሮ ቁጥር 2 መውሰድ ይኖርባቸዋል::
- ተጫራቾች የጨረታ ሣጥን ከመከፈቱ በፊት ለተወዳደሩባቸው ዕቃዎች ናሙና ከቢሮ መውሰድ ይኖርባቸዋል::
- አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉባቸውን ዕቃዎች በራሳቸው ትራንስፖርት ግዥ ፈጻሚው መሥሪያ ቤት ድረስ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል::
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
አድራሻ :- ጉርድ ሾላ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሕንፃ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 6
ለበለጠ መረጃ ፡- 0116-47-97-94/ 0116-47-95-78 ደውለጡ መጠየቅ ይችላሉ::
ፋክስ - 0116-45-08-79
ፖ.ሳ.ቁ - 13336
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
