ሆራይዘን አዲስ ጎማ ማ/ኃ/የተ/የግ/ማ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
የብረታ ብረት ጨረታ ሽያጭ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 02/2017
ሆራይዘን አዲስ ጎማ ማ/ኃ/የተ/የግ/ማ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
- ትልልቅ ያገለገሉ የኤሌክትሪክ ሞተሮች፤ ቤሪንጎች
- ልዩ ልዩ ያገለገሉ ቫልቮች፤ ፓይፖች
- ያገለገሉ ሞልዶች
- የማሽን አካሎች
- የብረታ ብረት ቁራጮች
- የብረት ፓሌትና የብረት አቃፊ ያላቸው የውሃ ሮቶዎች
በመሆኑም ፍላጎት ያላቸውን ተጫራቾች በሙሉ እንዲሳተፉ ይጋብዛል፡፡
በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች የሚከተሉትን ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆን አለባቸው፡፡
- የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ታኅሣሥ 24 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ በሥራ ቀናት የማይመለስ ብር 150 /አንድ መቶ ሃምሳ ብር/ በመክፈል ከኩባንያው የምርት ሽያጭ ቢሮ መግዛት እና ዕቃዎቹን ማየት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች መግዛት የሚፈልጓቸውን ዕቃዎች በጨረታ ሰነዱ ላይ የተገለጸውን ሲፒኦ በማስያዝ በዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ ላይ የእያንዳንዱን ዋጋ ከተጨማሪ እሴት ታክስ በፊት በግልጽ ሞልተው፣ ሙሉ ስማቸውንና አድራሻቸውን ጽፈው ከፈረሙበት በኋላ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ እስከ ታኅሣሥ 24 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ በሽያጭ ቢሮ ፊት ለፊት ባለው የጥበቃ በር ቁጥር 2 ቢሮ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ፡፡ የጨረታ ሳጥኑ በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 4፡05 ሰዓት ይታሸጋል፡፡ ጨረታው ታኅሣሥ 24 ቀን 2017 ዓ.ም ታኅሣሥ 24 ቀን 2017 ዓም ከጠዋቱ 4፡20 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግልጽ ይከፈታል፡፡
- ድርጅቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ ለተጨማሪ መረጃ፡- ንብረት አስተዳደር መምሪያ ቢሮ
ስልክ ቁጥር ፡- 011-442-15-55-/234 ወይም 0943880372 መጠየቅ ይቻላል፡፡
ሆራይዘን አዲስ ጎማ ማ/ኃ/የተ/የግ/ማ
