የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከየካ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ በተፃፈልን ደብዳቤ መሠረት የፌዴሬሽኑ ህንፃ በሚገኝበት አካባቢ ከወንጀል ለመከላከል ይረዳ ዘንድ የውጪ የደህንነት ካሜራ መግጠም ስለፈለገ በቀረበው Specification መሠረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
በድጋሚ የወጣ የደህንነት ካሜራ
ግዥ ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከየካ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ በተፃፈልን ደብዳቤ መሠረት የፌዴሬሽኑ ህንፃ በሚገኝበት አካባቢ ከወንጀል ለመከላከል ይረዳ ዘንድ የውጪ የደህንነት ካሜራ መግጠም ስለፈለገ በቀረበው Specification መሠረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
በዚህ መሠረት :-
- በጨረታው ለመወዳደር የምትፈልጉ ተጫራቾች የታደስ ንግድ ፍቃድ ያላቸው፤ የቲን እና ቫት ተመዝጋቢ የሆኑ::
- ተጫራቾች የጨረታውን ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ከረታ ሰነድ ጋር የሚያቀርቡትን ዕቃ የጠቅላላ ዋጋውን ቫትን ጨምሮ 2% አያይዘው የማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዶቻቸውን ዋናውንና ኮፒውን በታሽ ኤንቨሎፕ ማስታወቂያ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ለተከታታይ 10 የሥራ ቀናት በፌደሬሽኑ ቢሮ ቁጥር 5 ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአስረኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚያ ዕለት 4:30 ሰዓት በፌዴራሽ ቢሮ ቁጥር 5 (መሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል።
- ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን ዕቃዎች ከቫት ጋር ያለውን ዋጋ ማስቀመጥ ይጠበቅባቸዋል።
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ሰነድ (Specification) ከቢሮ ቁጥር 2 ውሰድ ይኖርባቸዋል፡፡
- አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፋቸውን ዕቃዎች በራሳቸው ትራንስፖርት ግዥ ፈጻሚው መሥሪያ ቤት ድረስ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው
አድራሻ :- ጉርድ ሾላ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሕንፃ 2 ፎቅ ቢሮ ቁጥር 6
ለበለጠ መረጃ ፡- 0116-47-97-94/ 0116-47-95-78 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
ፋክስ :- 0116-45-08-79 ፖ.ሣ.ቁ 13336
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
