Tender Detail

Tender Details

  • Company የግል ድርጅት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር
  • Address መገናኛ ቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፊት ለፊት ወይም መገናኛ ሕዳሴ ህንጻ ወረድ ብሎ : አዲስ አበባ ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 011 157 0333
  • Websitehttps://www.poessa.gov.et/
  • Deadline01 Feb 2025, 10:00 AM
  • magazine
  • Bid Document Price
  • opening date
  • Categories

የግል ድርጀት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር ከዚህ በታች የቀረቡትን ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡


 

የጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ማስታወቂያ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏

 

የግል ድርጀት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር ከዚህ በታች የቀረቡትን ዕቃዎች ማለትም

የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣

የጽህፈት መሣሪያዎች፣

ልዩ ልዩ የቢሮ መገልገያ መሳሪያዎች፤

የፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገድ አገልግሎት፣

የቦቴ ውሃ አቅርቦት አገልግሎት፣

የተሽከርካሪ ጎማዎች፣

የደንብ ልብስ፣

የጽዳት ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡

በዚሁ መሰረት ከዚህ በታች የተገለፀውን መስፈርት የሚያሟሉ ድርጅቶች በጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ እንዲካፈሉ ተጋብዘዋል፡፡

  1. በዘርፉ ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ እና በጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ለመሳተፍ የሚያስችል ማስረጃ (ክሊራንስ) ማቅረብ አለባቸው፡፡
  2. የተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ ተመዝጋቢ የሆነ እና የንግድ መለያ ቁጥር (TIN) ያላቸው መሆን ይኖርባቸዋል።
  3. ተጫራቾች የአቅራቢነት የምስክር ወረቀት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  4. የብቃት ማረጋገጫ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  5. ማንኛውም ተጫራች ጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ከተከፈተ በኋላ በጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ሰነድ ላይ የተገለጸውን ማንኛውንም ሁኔታዎች መለወጥ ወይም ማሻሻል አይችልም፡፡
  6. የሚገዙ ዕቃዎች በተሰጠው ስፔስፊኬሽን እና በናሙና መሰረት አሟልቶ ላልቀረበ ማንኛውም ሁኔታዎች ስህተት ቢፈጸም ኃላፊነቱ የተጫራች/ የአቅራቢው/ ድርጅት ይሆናል።
  7. ለጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ማስከበሪያ በባንክ በተመሰከረለት CPO /ሲፒኦ/ ወይም የባንክ ዋስትና በአስተዳደሩ ስም ማስያዝ ይኖርበታል፡፡
  8. ተጫራች የጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200/ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
  9. የጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ሰነዱን ማስታወቂያ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ በጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ 15 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን 16ኛው የስራ ቀን 400 ታሽጎ በዚሁ ዕለት 430 ሰዓት‍‍‌‍‍‍‌‍‍‍‍‌‍‌‍ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
  10. ተጫራቾች ለሚጫረቱባቸው የደንብ ልብስ፣ የጽ/መሳሪያዎች እና የጽዳት ዕቃዎች እና የተሽከርካሪ ጎማዎች ናሙና /ሳምፕል ጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ከመከፈቱ በፊት በአስተዳደሩ ንብረት ክፍል ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ዕቃዎቹ ሙሉ በሙሉ ኦሪጅናል መሆን አለባቸው፡፡
  11. ተጫራቾች የጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ሰነድ ዋናውንና ኮፒው ቴከኒክና ፋይናንስ በተናጥል በታሸገ ኤንቨሎፕ የድርጅቱን ማህተም ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡
  12. ለጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ የሚቀርበው ሰነድ ስርዝ ድልዝ የሌለበት ሆኖ የሚቀርበው ዋጋ በግልጽ መጻፍ ይኖርበታል። እንዲሁም በአስተዳደሩ ተዘጋጅቶ በጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ሰነድ ላይ ብቻ ዋጋ መሞላት አለበት፡፡
  13. አሸናፊ ድርጅት ላሸነፉባቸው ዕቃዎች ከጠቅላላ ዋጋ 10/100 ለድርጅቱ ውል ማስከበሪያ ማስያዝ ይኖርበታል።
  14. ጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ አሽንፎ በወቅቱ ውል ለማሰር ፈቃደኛ ያልሆነ ተጫራች ያስያዘው የጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ዋስትና ለአስተዳደሩ ገቢ ይደረጋል፡፡
  15. ተጫራቾች የፍሳሽ ማስወገድ አገልግሎት እና የቦቴ ውሃ አቅርቦት ግዥ ለአንድ ዓመት ውል በመያዝ የሚሰራ መሆኑን ማወቅ ይኖርባቸዋል፡፡
  16. አስተዳደሩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

 

አድራሻችን ፡- አዲስ አበባ መገናኛ ቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፊት ለፊት ወይም

የአስተዳደሩ ዋና /ቤት 11 ፎቅ

ለበለጠ ማበራሪያ ስልክ ቁጥር ፡-251-111-56 88 90/0111 53 03 73 መደወል ይችላሉ፡፡

.

ግዥው ዓይነት

የጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ቁጥር

የጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ማስከበሪያ የገንዘብ መጠን

ምርመራ

ሎት 1

የውሃ ፓምፕ አቅርቦት እና ቴክላ የሚያስፈልገውን ዕቃዎች በማቅረብ 15(አስራ አምስት ፎቅ ላለው ህንፃ)

እና 0012/2017

100,000.00 /አንድ መቶ ሺህ ብር ብቻ/

 

ሎት 2

ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች

0013/2017

50,000.00 /አምሳ ሺህ ብር ብቻ

 

ሎት 3

የጽህፈት እና አላቂ የቢሮ ዕቃዎች

014/2017

30,000.00/ሰላሳ ሺህ ብር ብቻ/

 

ሎት 4

ልዩ ልዩ ቢሮ መሳሪያዎች

015/2017

5,000 /አምስት ሽህ ብር ብቻ/

 

ሎት 5

የፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገድ አገልግሎት

016/2017

5,000 /አምስት ሺህ ብር ብቻ/

 

ሎት 6

የደንብ ልብስ ግዥ

017/2017

10,000/አስር ሺህ ብር ብቻ/

 

ሎት 7

የጽዳት ዕቃዎች

018/2017

5,000 /አምስት ሺህ ብር ብቻ/

 

ሎት 8

የተሽከርካሪ ጎማዎች

019/2017

30,000 /ሰላሳ ሺህ ብር ብቻ/

 

ሎት 9

ንጽህ የቦቴ ውሃ የሚያቀርብ

020/2017

5,000 /አምስት ሺህ ብር ብቻ/

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

የግል  ድርጅቶች  ሠራተኞች  ማህበራዊ  ዋስትና  አስተዳደር

 

Save Tender