የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶች ለማንቃሳቀስ የምርት መያዣ ፕላስቲክ ሳጥን ግዥ የመንግስትን ግዥ መስፈርቶች የሚያሟሉ እና በዘርፉ ከተሰማሩ ህጋዊ ድርጅቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በድጋሚ የወጣ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የግዥው መለያ ቁጥር:- ኢንሥኮ-ማዕከል ግዥ ብግጨ 11/2017
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶች ለማንቃሳቀስ የምርት መያዣ ፕላስቲክ ሳጥን ግዥ የመንግስትን ግዥ መስፈርቶች የሚያሟሉ እና በዘርፉ ከተሰማሩ ህጋዊ ድርጅቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
- የምርት መያዣ የፕላስቲክ ሳጥን ብዛት 10,000.00 (አስር ሺህ ብር)
- ተጫራቾች በዘርፉ ለ2017 በጀት ዓመት የታደሰ የንግድ ፈቃድ፤ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት፤ የአቅራቢነት ምዝገባ የምስክር ወረቀት፤ በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል ከግብር ሰብሳቢ መ/ቤት የተሰጠ ወቅታዊ የድጋፍ ደብዳቤ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ የምስክር ወረቀት እና የግብር ከፋይ ምዝገባ ሰርተፊኬት ማቅረብ ይኖርባቸዋል። እነዚህ ሰነዶች በቴክኒካል ፕሮፖዛል ፖስታ ውስጥ ታሽገው መቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ከላይ የተገለጹትን ሰነዶች ከጨረታ ሰነድ ማቅረቢያው ቀነ ገደብ በፊት ማቅረብ አለባቸው። ከጨረታ መክፈቻው ቀን በኋላ የተገኘ ማስረጃ ተቀባይነት የለውም።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 450.00 (አራት መቶ ሃምሳ ብር) በመክፈል ከጥር 13 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ዘወትር ከሰኞ እስከ አርብ ከጠዋቱ 2፡00-6፡00 ሰዓት እንዲሁም ከሰዓት ከ7፡00 10፡30 ሰዓት እንዲሁም ቅዳሜ ከጠዋቱ 2፡00 -6፡00 ሰዓት ድረስ ማመልከቻ በመያዝ ብሎክ 1 ቢሮ ቁጥር 206 ድረስ በመቅረብ መግዛት ይችላሉ። (አድራሻው ከስር ተገልጿል።)
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን እስከ ጨረታው መዝጊያ ዕለት እስከ ጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም 4፡30 ድረስ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ብር 10,000.00 (አስር ሺህ ብር) በሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና በኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ስም አሰርተው ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር ማቅረብ አለባቸው፡፡ ኢንሹራንስ ቦንድና ቼክ ተቀባይነት የላቸውም። የጨረታ ማስከበሪያው በቴክኒካል ፐሮፖዛል ፖስታ ውስጥ ወይም ለብቻው ታሽጎ መቅረብ ይኖርበታል ።
- ተጫራቾች ቴክኒክ እና ፋይናንስ ሰነድ በግልጽ ከፋፍለው በተለያየ ኤንቨሎፕ ለየብቻ አሽገው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው ጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም 4፡30 ተዘግቶ በዚሁ ዕለት 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በዋናዉ መስሪያ ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል።
- ከዋና የመወዳደሪያ ሀሳብ (ኦሪጅናል) በተጨማሪ የሚፈለጉ ኮፒዎች ብዛት 1 (አንድ) ነው፡፡
- አሸናፊው ድርጅት የውል ማስከበሪያ መጠን ለአሸነፉበት የምርት መያዣ ፕላስቲክ ሳጥን ጠቅላላ ዋጋ 10 ፐርሰንት በሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና በኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ስም አሰርተው ውሉን የሚፈጽሙ ይሆናል።
- ተጫራቾች የምርት መያዣ ፕላስቲክ ሳጥን ናሙና መቅረብ አለበት። የሚቀርበው ናሙና በተያያዘው ዝርዝር የፍላጎት መግለጫ ተዘጋጅቶ መቅርብ ያለበት ሲሆን ከተቀመጠው መጠን በላይ ሆነ በታች የሚቀርብ ናሙና ተቀባይነት የለውም።
- ኮርፖሬሽኑ ጨረታውን በከፊልም ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለማንኛውም ማብራሪያ በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ በመደወል መጠየቅ ይቻላል።
አድራሻ ፡-
ደብረዘይት መንገድ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጠመንጃ ያዥ ቅርጫፍ ፊት ለፊት
ፖ.ሳ.ቁ 7858
ስልክ ቁጥር ፡- 011 4167345 / 011 4669336
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን
