የጂንካ ማረሚያ ተቋም ለ2017 በጀት ዓ.ም ለህግ ታራሚዎች ለምግብ አገልግሎት የሚውል በቆሎ፣ ቀይ ሽንኩርት፣ ጨው በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የጂንካ ማረሚያ ተቋም ለ2017 በጀት ዓ.ም ለህግ ታራሚዎች ለምግብ አገልግሎት የሚውል በቆሎ፣ ቀይ ሽንኩርት፣ ጨው በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም በዚሁ ዘርፍ የተሰማራችሁ ተጫራቾች (ነጋዴዎች) ከዚህ በታች በተገለፀው ዝርዝር መስፈርት ቀርባችሁ መወዳደር ትችላላችሁ፡፡
የተጫራቾች መስፈርት ፡-
- በዘርፉ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያለው (ያላት)
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያለውና መረጃውን ማቅረብ የሚችል
- የዘመኑን ግብር ስለመከፈሉ ማረጋገጫ የሚያቀርብ
- የታደሰ የንግድ ፍቃድ መረጃ ማቅረብ የሚችል
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆነ
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ (50,000 ) ሃምሳ ሺ ብር በባንክ በተረጋገጠ በCPO (በጥሬ ገንዘብ) በቅድሚያ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- የጨረታ ሰነድ የሚሸጥበት ዋጋ 20 ብር /ሃያ ብር/
- የጨረታ ሰነድ የሚገኝበት ቦታ ጂንካ ማረሚያ ተቋም ቢሮ ቁጥር 4
- የጨረታ ሰነድ ሽያጭ የሚካሄደዉ ጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 (አስራ አምስት) ቀናት ሲሆን በ16ኛዉ ቀን ከጠዋቱ 2፡00 እስከ 4፡00 ሰዓት በጨረታ ሳጥን ውስጥ የሚገባ ሆኖ 4፡30 ላይየሚከፈት ይሆናል ። ሆኖም 16ኛ ቀን የሥራ ቀን ከልሆነ በቀጣይ የሥራ ቀን የሚከፈት ይሆናል፡፡
- የእቃ ርክክብ የሚፈፀምበት ቦታ ጂንካ ማረሚያ ተቋም
ማሳሰቢያ :- ተቋሙ የተሻለ አማራጭ ካገኘ በሙሉ ወይም በከፊል ጨረታውን የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ስልክ ቁጥር ፡- 0468759067
የጂንካ ማረሚያ ተቋም
