የስልጤ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለዞኑ ውሃ ማእድንና ኢነርጂ መምሪያ ፓምፕና ሞተር ከነሙሉ አክሰሰሪው እና የውሃ ቱቦ ከነመገጣጠሚያው በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የስልጤ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለዞኑ ውሃ ማእድንና ኢነርጂ መምሪያ ፓምፕና ሞተር ከነሙሉ አክሰሰሪው እና የውሃ ቱቦ ከነመገጣጠሚያው በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም የዘመኑን የታደሰ የንግድ ስራ ፍቃድ ማቅረብ የሚችሉ
- የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ማቅረብ የሚችል
- የአቅራቢነት ምዝገባ ሠርተፊኬት ማቅረብ የሚችል
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ
- የዘመኑን የታደሰ ንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚችሉ
- የጨረታ ማስከበሪያ ብር 20000 /ሃያ ሺህ/ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ ጋራንቲ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ሰነዱን ከስልጤ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በመቅረብ ሰነዱን ብር አንድ መቶ በመክፈል መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን የጨረታ ሰነዱን በሚገባ በመሙላት አንድ ኦርጂናልና 1 ኮፒ ለየብቻ በሰም በታሽገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ይህ ማስታውቂያ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ በስልጤ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ የጨረታ ሳጥኑ በ15ኛው ቀን በ8፡00 ሰዓት ታሽጎ 8፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ 15ኛው ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ያለመገኘት ጨረታውን ከመከፈት እያስቀረውም።
መምሪያው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0467710586/082/083
የስልጤ ዞን ፋይናንስ መምሪያ
ወራቤ
