ድርጅታችን በመከኒሳ ዋና መስሪያ ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ ከሚገኙት የሞላሰስ ማከማቻ ታንከር ኢፖክስ ቅብ (Epoxy Painting) በጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 040/2017 ዓ.ም
ድርጅታችን በመከኒሳ ዋና መስሪያ ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ ከሚገኙት የሞላሰስ ማከማቻ ታንከር ኢፖክስ ቅብ (Epoxy Painting) በጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም ተጫራቾች ፡-
- የታደሰ ፍቃድና የዘመኑ ግብር ለመክፈላችሁ መረጃ ማቅረብ ይኖርባችኋል፤
- የማይመለስ ቫትን አካቶ በብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጨረታ ሠነዱን መከኒሳ በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ገንዘብ ቤት ቢሮ ቁጥር 004 በመቅረብ መግዛት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፤
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዶቻቸውን ቴከኒካል እና ፋይናንሻል ሰነድ ኦሪጅናል እና ፎቶ ኮፒ ለየብቻው በታሸገ ኤንቨሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ለጨረታ ዋስትና የሚሆን የሚያቀርቡትን አጠቃላይ ዋጋ 2% በሲፒኦ ለብቻው በኤንቨሎፕ በማሸግ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፤
- ተጫራቾች የሚያስገቧቸውን ሠነዶች መጋቢት 19 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት መከኒሳ በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ግዥ ቢሮ ቁጥር 503 ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው በዚያው ዕለት ከጠዋቱ 4፡15 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፤
- ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
ፖ.ሣ.ቁ. 3516 ስልክ ቁጥር 011 369 0563 ፋክስ 011 5 513299
ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ
