ድርጅታችን በአቃቂ ክፍለ ከተማ የሚገኘውን የድርጅቱን የቫሊቦል መጫወቻ ሜዳ ኢፖክሲ ንጣፍ በጨረታ አወዳድሮ ለማስነጠፍ ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 039/2017 ዓ.ም
ድርጅታችን በአቃቂ ክፍለ ከተማ የሚገኘውን የድርጅቱን የቫሊቦል መጫወቻ ሜዳ ኢፖክሲ ንጣፍ በጨረታ አወዳድሮ ለማስነጠፍ ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም መወዳደር የምትፈልጉ ተጫራቾች -
- የታደሰ ንግድ ፍቃድና የዘመኑን ግብር ለመክፈላችሁ መረጃ ማቅረብ ይኖርባችኋል፤
- ቫትን አካቶ የማይመለስ ብር 115.00 /አንድ መቶ አስራ አምስት/ በመክፈል ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጨረታ ሠነዱን መካኒሳ በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ገንዘብ ቤት ቢሮ ቁጥር 004 በመቅረብ መግዛት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፤
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዶቻቸውን ቴከኒካል እና ፋይናንሻል ሰነድ “ኦሪጅናል” እና “ፎቶ ኮፒ ለየብቻው በታሸገ ኤንቨሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋውን 2 በመቶ በሲፒኦ ለብቻው በኤንቨሎፕ በማሸግ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፤
- ተጫራቾች የሚያስገቧቸውን ሠነዶች እስከ መጋቢት 18 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት መካኒሳ በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ግዥ ቢሮ ቁጥር 503 ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው በዚያው ዕለት ከጠዋቱ 4፡15 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
ስልክ: 011 369 0563 ፋክስ: 011 5 513299
ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ
