Tender Detail

Tender Details

  • Company በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የዝቋላ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት
  • Address በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዝቋላ ወረዳ፡ አማራ ክልል ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 0334620050/53/49
  • Website
  • Deadline15 Apr 2025, 12:00 AM
  • magazine
  • Bid Document Price
  • opening date2025-04-15 00:00:00
  • Categories Building Materials , Construction Materials And Raw Materials

በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የዝቋላ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት አማካኝነት በ2017 በጀት በካፒታል በጀት በወረዳው ለሚያስገነባው G+2 የአስተዳደር ሕንፃ የተለያዩ የግንባታ ግብአቶችን ወይም የሕንፃ መሣሪያዎች በአገር አቀፍ ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡


 

የአገር አቀፍ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ


 

በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የዝቋላ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት አማካኝነት በ2017 በጀት በካፒታል በጀት በወረዳው ለሚያስገነባው G+2 የአስተዳደር ሕንፃ የተለያዩ የግንባታ ግብአቶችን ወይም የሕንፃ መሣሪያዎች በአገር አቀፍ ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በዚህም መሰረት የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው

  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን /ያላቸው

  3. ለመንግሥት የሚጠበቅባቸውን የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆናቸውን መረጃ ማቅረብ የሚችሉ

  4. 200,000 /ሁለት መቶ ሺ ብር/ በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ መሆን አለበት፡፡

  5. ተጫራቾች ጨረታው ላይ ለመሳተፍ ከላይ ከተ.1 እስከ 4 የተጠቀሱትን እና ሌላም መረጃ ፎቶ ኮፒ በማድረግ ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው በሁለት ኦርጅናል እና ኮፒ ብለው ማቅረብ አለባቸው፡፡

  6. ዝርዝር /ስፔስፊኬሽን / ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡

  7. /ቤቱ ካስቀመጠው ውጪ በራሱ ጊዜ እስፔስፊኬሽን የጨመረና የቀነስ ወይም ያስቀመጠ ከውድድሩ ውጭ ይሆናል፡፡

  8. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 200 /ሁለት መቶ ብር/ ብቻ በመክፈል ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት በዝ//ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 10 በመምጣት ጨረታ ሰነዱን መግዛት የምትችሉ መሆኑን እና 16ኛው ቀን 230-630 በተዘጋጀው ሣጥን በማስገባት በዚያው ቀን 800 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም በዝ//ገንዘብ ጽ/ቤት በግልጽ ይከፈታል፡፡

  9. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሚወዳደሩበትን የዕቃውን ጠቅላላ ዋጋ 2 % በጥሬ ገንዘብ ወይም በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /በሲፒኦ/ ማስያዝ አለበት፡፡

  10. ተጫራቶች ከሚወዳደሩበት ሰነድ ላይ ከአንዱ ዋጋው እና ጠቅላላ ዋጋው ላይ ስርዝ ድልዝ ያደረገ ከጨረታው /ከውድድሩ ውጪ ይሆናሉ፡፡

  11. ጨረታው ተከፍቶ አሸናፊ ከሆኑ የጨረታውን ውል ማስከበሪያ ያቀረቡትን ጠቅላላ ዋጋ ድምር 10% በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ በተረጋገጠ የባንክ ትዕዛዝ /../ በማስያዝ አሸናፊ መሆናቸው ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ከ5 የሥራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ውል መውሰድ አለበት፡፡

  12. /ቤቱ በጨረታው ዙሪያ የተሻለ አማራጭ ካገኘ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

  13. ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በዓል ወይም የመንግሥት ሥራ ዝግ ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀንና ሰዓት በተመሳሳይ ጊዜ ይከፈታል፡፡

  14. ማንኛውም ተጫራች ከኦርጅናል ሰነዱ ላይ የንግድ ፍቃዱን ኮፒ አድርጎ ፖስታው ላይ የማያስገባ ወይም ኮፒ አድርጎ ፖስታው ላይ ሳያስገባ ውጭ ላይ የተወ ከውድድር ውጪ የሚሆን መሆኑ ይታወቅ፡፡

  15. ውድድሩ በጠቅላላ ድምር /ሎት/ መሆኑ መታወቅ አለበት፡፡


 

በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የዝቋላ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

 

Save Tender