የአራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2017 በጀት አመት የሚወገዱ ንብረቶች 1. ቁርጥራጭ ብረታብረት በkg የሚመዘን፤ 2. የብር ካዝና ብዛት 2 /ሁለት/፤ 3. የባንዲራ መስቀያ ብረት በkg የሚመዘን አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 1/2017
የአራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2017 በጀት አመት የሚወገዱ ንብረቶች 1. ቁርጥራጭ ብረታብረት በkg የሚመዘን፤ 2. የብር ካዝና ብዛት 2 /ሁለት/፤ 3. የባንዲራ መስቀያ ብረት በkg የሚመዘን አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል። ስለሆነም ከዚህ በታች የተዘረዘሩ መስፈርቶችን የምታሟሉ መጫረት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
- ተጫራቾች በአቅራቢ ዝርዝር የተመዘገቡ መሆኑን እና የዘመኑ ግብር የከፈሉ መሆናቸውን የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- የታደሰ የንግድ ፈቃድና የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የሚያስገቡት ዋጋ ቫትን ያካተተ መሆን አለበት ::
- የጨረታ ሰነዱ የመወዳደሪያ ዋጋ በሙሉ ታሽጎ ለጨረታ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታው ማስታውቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ የማይመለሰ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ ብቻ በመክፈል ከወረዳ 5 ፋይናንስ ጽ/ቤት የጨረታ ሰነዱን መግዛት የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
- ጨረታው ከወጣበት ቀን አንስቶ በ11ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት የሚታሽግ ሲሆን 4፡30 ሰዓት ሳጥኑ የሚከፈት ይሆናል፡፡
- የመወዳደሪያ ዋጋ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ወስጥ ማስገባት የምትችሉ ሲሆን ጨረታው የሚከፈተው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ይሆናል ፡፡
- ተጫራቾች ዋጋቸውን በወሰዱት የጨረታ ሰነድ ላይ ብቻ መሙላት ይጠበቅባቸዋል፡፡ 1
- የጨረታ ዋስትና በሞሉት ዋጋ 2% ሲፒኦ ብቻ ሲሆን የምንቀበለው ቼከ አንቀበልም በተጨማሪም ተጫራቾች አሸናፊ ሆነው ሲቀርቡ አሸናፊ የሆኑበትን 10% ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- መስሪያቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ማሳሰቢያ፦ ተጫራቾች ለሚኖራቸው ጥያቄ መረጃ ለማግኘት ቢፈልጉ በስልክ ቁጥር 011266384 በመደወል መጠየቅ ይችላሉ፡፡
አድራሻ፡- ፒያሳ ገዳም ሰፈር ከጊዮርጊስ ጀርባ ወደ ዳክስን መሄጃ ወረዳ 5 ፋይናንስ ጽ/ቤት 2ኛ ፎቅ
የአራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት
