የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የጃንሜዳ ስታፍ ኮሌጅ G+10 /17-06B/ህንፃ ግንባታ ፕሮጀክት Supply and apply Cementious water proofing ዝርዝር ስራውና መግለጫው በጨረታ ሰነዱ ላይ በተገለፀው መሰረት ተጫራቾችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር DCE/SC/137/2017
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የጃንሜዳ ስታፍ ኮሌጅ G+10 /17-06B/ህንፃ ግንባታ ፕሮጀክት Supply and apply Cementious water proofing ዝርዝር ስራውና መግለጫው በጨረታ ሰነዱ ላይ በተገለፀው መሰረት ተጫራቾችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም፡-
- ተጫራቾች ህጋዊ የንግድ ፈቃድ የላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ እና ለተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበትን የግብር መለያ ቁጥር እንዲሁም በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል የታደሰ ታክስ ክሊራንስ አቅራቢነት ሊስት የተመዘገቡ ስለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሚያቀርቡት ገንዘብ ብር 50,000.00 /ሀምሳ ሺህ ብር/ ሲሆን CPO ወይም በባንክ Bid Guarantee መሆን አለበት፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 200.00 ብር /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ዘወትር በስራ ሰዓት ቅዳሜን ጨምሮ ተከታታይ 15 የስራ ቀናት ጃንሜዳ ስታፍ ኮሌጅ ፕሮጀክት ገንዘብ ያዥ ቢሮ በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበት ዋጋ በታሸገ ኤንቨሎፕ እስከ ሚያዚያ 20/2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ሚያዚያ 20/2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በፕሮጀክቱ ቢሮ ይከፈታል፡፡
- ፕሮጀከቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ፡- የቀጥታ ስልክ ቁጥር 0118-95-98-10/0118121352
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርኘራይዝ የጃንሜዳ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ ኘሮጀክት 17-06B
