በአሮሚያ ግብርና ኅብረት ሥራ ማኅበራት ፌዴሬሽን ኃላ.የተ አሰላ ብቅል ፋብሪካ ጥራትና ደረጃቸውን የጠበቀ የብቅል ምርት መቋጠሪያ ባለ 50 ኪ.ግ አቅም እና ፍላጎት ያላቸውን ድርጅቶች በግልፅ ጨረታ በማወዳደር ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የግዥ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡ NCB/OACFLTD/AMF/09/2017
በአሮሚያ ግብርና ኅብረት ሥራ ማኅበራት ፌዴሬሽን ኃላ.የተ አሰላ ብቅል ፋብሪካ ጥራትና ደረጃቸውን የጠበቀ የብቅል ምርት መቋጠሪያ ባለ 50 ኪ.ግ አቅም እና ፍላጎት ያላቸውን ድርጅቶች በግልፅ ጨረታ በማወዳደር ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም በጨረታው ለመወዳደር የሚፈልጉ ድርጅቶች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት አለባቸው::
- ተጫራቾች የ2017 የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ በግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /IN/ ያላቸው እና የተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ተመዝጋቢ ስለመሆናቸው ሕጋዊ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር ብቻ) በፋብሪካችን አካውንት በኢትዮጰያ ንግድ ባንክ 1000257808697 ወይም በኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ 1000043405229 በመክፈል ገቢ በማድረግ/፡፡
- ዘወትር በሥራ ሰዓት ከሰኞ እስከ ዓርብ ጠዋት 2፡00-6፡00 ከሰዓት በኋላ 7፡00-10፡00 ሰዓት ድረስ ከጀርመን አደባባይ ወደ ሚካኤል አደባባይ በሚወስደው መንገድ ላይ ሚካኤል ቤ/ክርስቲያን አጠገብ በሚገኘው የኦሮሚያ ግብርና ኅብረት ሥራ ማኅበራት ፈዴሬሽን ሕንፃ ስድስተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 6 ወይም አሰላ- ቁሉምሳ ከሚገኘው ፋብሪካችን ቢሮ ቁጥር 003 ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን በፖስታ በማሸግ አዲስ አበባ በሚገኘው የፋብሪካችን ዋና መ/ቤት በአሮሚያ ግብርና ኅብረት ሥራ ማኅበራት ፌዴሬሽን ኃላየተ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ከታች ከተጠቀሰው የመዝጊያ ሰዓት በፊት ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ከመወዳደሪያ ሰነዳቸው ጋር ብር 200,000.00 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ በተመሰከረለት ሲፒኦ (CPO) ብቻ በማስያዝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ከመወዳደሪያ ሃሳባቸው ጋር በተቀመጠው ዝርዝር መስፈርት መሰረት ናሙና ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን ጨረታው በጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 21 ቀናት ክፍት ሆኖ የሚቆይ ሲሆን በ22ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ተዘግቶ ከጠዋቱ 5፡00 ሰዓት ላይ ለመገኘት በሚሹ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት አዲስ አበባ በሚገኘው የፋብሪካችን ዋና መ/ቤት የኦሮሚያ ግብርና ኅብረት ሥራ ማኅበራት ፌዴሬሽን ኃላ.የተ 7ኛ (ሰባተኛ) ፎቆ ላይ በሚገኘው የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፣ የመከፈቻው ቀን ቅዳሜ እና እሁድ ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
- ፋብሪካው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ተጫራቾች በጨረታ ማስታወቂያና በተጫራቾች መመሪያ ላይ ግልጽ ያልሆነ ነጥብ ካለና ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ በስልከ ቁጥር፡- 09-65-65-04-81/09-65-65-02-85 022 331 17 99 በሥራ ሰዓት ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የኦሮሚያ ግብርና ኅብረት ሥራ ማኅበራት ፌዴሬሽን ኃላ.የተ አሰላ ብቅል ፋብሪካ
