ኮርፖሬሽናችን ውል ወስዶ ለሚገነባው ለጋሽና ብልባላ-ሰቆጣ አስፓልት መንገድ ፕሮጀክት አገልግሎት የሚውል የላብራቶሪ እቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ኅኮኮ 17/2017
ኮርፖሬሽናችን ውል ወስዶ ለሚገነባው ለጋሽና ብልባላ-ሰቆጣ አስፓልት መንገድ ፕሮጀክት አገልግሎት የሚውል የላብራቶሪ እቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
|
ተ.ቁ |
የእቃው አይነት |
ምርመራ |
|
1 |
የላብራቶሪ እቃዎች ግዥ |
መጠኑ ጨረታ ሰነዱ ላይ ተገልጿል |
ስለዚህ ከዚህ በታች የተገለፁትን የጨረታ መወዳደሪያ መስፈርቶችን የሚያሟሉ ማንኛውም አቅራቢ ድርጅት በጨረታው መወዳደር ይችላል፡፡
- በዘርፍ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸው፤ የተ.እ.ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ፣ የግብር ከፋይነት ምዝገባ ሰርተፍኬት ያላቸው፣ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ያላቸው እንዲሁም በዘርፉ በአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገቡ እና ግብር ግዴታቸውን ስለመወጣታቸው የሚገልፅ የግብር ክሊራንስ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው::
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚውል በድርጅታችን ስም “ኅብር ኮንስትራክሽን ኮርፓሬሽን" (Hibir construction corporation) በሚል 190 ቀናት ፀንቶ የሚቆይ ሲ.ፒ.አ ወይም ያለቅድመ ሁኔታ እንደተጠየቀ የሚከፈል ባንክ ጋራንቲ የተ.እ.ታ ታክስን ጨምሮ 100,000 (አንድ መቶ ሺህ) ብር ማስያዝ አለባቸው::
- ኮርፓሬሽናችን አሸናፊውን ተጫራች ድርጅት በሚመርጥበት ጊዜ የሚገዛውን እቃ መጠን እንደ አስፈላጊነቱ እስከ 50% ሊቀንስ ወይም ሊጨምር ይችላል፡፡
- ተወዳዳሪ ድርጅቶች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን ቴክኒካል ሰነድ ቅጂና ዋና እና ፋይናንሻል ሰነድ ቅጂ እና ዋና ለየብቻ በፖስታ በማዘጋጀት እና የጨረታ ማስከበሪያውን በአንድ ፖስታ ለብቻ በማድረግ በአንድ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 20 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን ባህር ዳር ከተማ ከሚገኘው ዋና መ/ቤታችን ኅብር ኮንስትራክሽን ኮርፓሬሽን (Hibir construction corporation) ዋናው መ/ቤት አማራ ፓይፕ ፋብሪካ ፊት ለፊት ግዥ ቢሮ በመቅረብ ለጨረታው በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው::
- ጨረታው በ20ኛው ቀን 4፡00 ተዘግቶ በዚሁ ቀን 4:30 ይከፈታል፡፡ ነገር ግን የመክፈቻ ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
- የጨረታውን ዝርዝር መግለጫ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት የሚችሉ ሲሆን እያንዳንዱ ሰነዱን መሸጫ የማይመለስ ብር 300.00 /ሶስት መቶ ብር ብቻ/ በመክፈል ኀበር ኮንስትራክሽን ኮርፓሬሽን ፋይናንስ የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 23 መግዛት ይችላሉ፡፡
- ኮርፓሬሽኑ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 058-320-35-76 መደወል ይችላሉ፡፡
ኅብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን
