ሐበሻ ሲሚንቶ አክሲዮን ማኅበር ሆለታ ከተማ አቅራቢያ ለሚገኘው ሲሚንቶ ፋብሪካው በግብዐትነት የሚውል ጥሬ እቃ ጂፕሰም ፋብሪካው ድረስ ማቅረብ የሚችሉ ሕጋዊ ፈቃድ ያላቸውን ድርጅቶችን በጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል።
ሐበሻ ሲሚንቶ
HABESHA CEMENT
የሲሚንቶ ግብአት (ጂፕሰም) አቅርቦት
ጨረታ ማስታወቂያ
Procurement bld No. 01/ Raw material (Gypsum) Supply Service/2025
ሐበሻ ሲሚንቶ አክሲዮን ማኅበር ሆለታ ከተማ አቅራቢያ ለሚገኘው ሲሚንቶ ፋብሪካው በግብዐትነት የሚውል ጥሬ እቃ ጂፕሰም ፋብሪካው ድረስ ማቅረብ የሚችሉ ሕጋዊ ፈቃድ ያላቸውን ድርጅቶችን በጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል።
ተጫራቾች የአንድ ቶን ጂፕሰም ለማቅረብ ማጓጓዣን ጨምሮ የሚሰጡትን ዋጋ በፖስታ አሽገው ለግዢ እና አቅርቦት መምሪያ እስከ ግንቦት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ማቅረብ የሚችሉ ሲሆን ጨረታው በዕለቱ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን እንዲሁም የጨረታ ማስከበሪያ ብር 100,000 (አንድ መቶ ሺህ ብር) በሲፒኦ ወይንም የባንክ ጋራንቲ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዶቻቸውን ከላይ እስከተጠቀሰው ቀንና ሰዓት ድረስ ብቻ ከታች በተመለከተው አድራሻ ማቅረብ የሚችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ማሳሰቢያ
- ተጫራቾች የሚያቀርቡት ጅፕሰም ቴክኒካዊ ግምገማ የሚደረግበት መሆኑ እንደተተጠበቀ ሆኖ የሚከተሉትን ቴክኒካዊ መመዘኛ ሊያሟላ ይገባዋል።
|
የጥራት መለኪያ መስፈርት |
በፑሚስ ውስጥ ሊኖር የሚገባው መጠን |
|
መጠን (Size) |
<250 |
|
የሰልፌት መጠን (SO3%) |
35% |
- ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው።
- ተጫራቾች ሕጋዊ የሆነ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የፈቃዳቸውን ኮፒ እንዲሁም የዘመኑን ግብር የከፈሉ ስለመሆናቸው ከመወዳደሪያ ሰነዳቸው ጋር አብረው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ለአንድ ቶን የጅፕሰም ግብአት ለማቅረብ የሚሰጡትን ዋጋ ከነማጓጓዣው ተጨማሪ እሴት ታክስን ሳይጨምር በሚከተለው መልኩ ዋጋቸውን ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
|
የግብዐቱ ዓይነት |
መድረሻ |
መለኪያ |
የአንዱ ዋጋ (የተ.ዕ.ታን ሳይጨምር) |
|
ጂፕሰም |
ሐበሻ ሲሚንቶ ፋብሪካ |
ቶን |
|
- አሸናፊዊው ተጫራች ውጤቱ በተገለጸለት ባሉት ሶስት ተከታታይ ቀናት ውስጥ ሁለት መኪና የጥሬ እቃ ናሙና ለቴክኒካል ምርመራ የማቅረብ ግዴታ አለበት። ተጫራቹ በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ናሙናውን ማቅረብ ካልቻለ የጨረታ ማስከበሪያው የሚወረስ ይሆናል።
- በቀረበው ናሙና ላይ የተገኘው የላብራቶሪ ውጤት ቴክኒካል መመዘኛውን የሚያሟላ ሆኖ ከተገኘ ተጫራቹ በሶስት የስራ ቀናት ውስጥ የውል ስምምነት የሚፈጽም ይሆናል።
- ኩባንያው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በማንኛው ጊዜ በሙሉም ሆነ በከፊል ጨረታውን የመስረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡ አሮጌው ቄራ ከንግድ ማተሚያ ቤት ጀርባ ጌታ አስ ኢንተርናሽናል ሕንፃ 7ኛ ፎቅ
ስልክ: 0944122311/0912850906
ሐበሻ ሲሚንቶ አ.ማ
