በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የአዳሚ ቱሉ የፀረ-ተባይ ማዘጋጃ ፋብሪካ ያገለገሉ ንብረትነታቸው የአዳሚ ቱሉ የፀረ-ተባይ ማዘጋጃ ፋብሪካ የሆኑትንና ዝርዝር መግለጫቸው ከዚህ በታች የተሰጡትን ንብረቶች ባሉበት ቦታና ሁኔታ በግልጽ ጨረታ ቁጥር APPF/SP/03/17 አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
በድጋሜ የወጣ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የአዳሚ ቱሉ የፀረ-ተባይ ማዘጋጃ ፋብሪካ ያገለገሉ ንብረትነታቸው የአዳሚ ቱሉ የፀረ-ተባይ ማዘጋጃ ፋብሪካ የሆኑትንና ዝርዝር መግለጫቸው ከዚህ በታች የተሰጡትን ንብረቶች ባሉበት ቦታና ሁኔታ በግልጽ ጨረታ ቁጥር APPF/SP/03/17 አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
- ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችና መለዋወጫዎች
- የፎርክሊፍት መለዋወጫ እቃዎች ብዛት የተለያየ ፣
- የተለያዩ ያገለገሉ የልብስ ስፌት (የአልጋ አጎበር ስፌት) ማሽኖችና መለዋወጫዎች፣
ስለሆነም በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ማንኛውም ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩ መስፈርቶችን በሟሟላት መዳደር ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆናቸውን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸው፤
- ተጫራቾች ስለ ጨረታው ዝርዝር ሁኔታ የሚገልፀውን ሰነድና መመሪያ እንዲሁም የጨረታ ዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ አዳሚ ቱሉ ባለው የፋብሪከው ዋና መስሪያ ቤት ንግድ መምሪያ ቢሮ ወይም አዲስ አበባ ቦሌ ሩዋንዳ ጅቡቲ ኢምባሲ ፊትለፊት ከሚገኘው ማስተባበሪያ ቢሮ የማይመለስ ብር 500.00 (አምሰት መቶ ብር) በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ለተሽከርካሪ እና ለሌሎች ንብረቶች የሚገዙትን የጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ (10%) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ከጨረታ ሰነዱ ጋር በማያያዝ ለዚሁ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ሰነድ ገዝተው ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ቀናት ከጠዋቱ 2፡00 እስከ 10፡00 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ ንብረቱን አዳሚ ቱሉ ፋብሪካ በአካል በመሄድ መመልከት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዶች በሰም በታሸገ ኢንሸሎፕ በማድረግ ለጨረታው የተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ከጨረታው መዝጊያ ሰዓት በፊት ማስገባት ይጠበቅባቸዋል።
- ጨረታው እስከ ግንቦት 21 ቀን 2017 ዓ.ም ለተከታታይ የስራ ቀናት ክፍት ሆኖ የሚቆይ ሲሆን ግንቦት 21 ቀን 2017 ዓ.ም ጠዋት 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ እለት ከጧቱ በ4፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት አዲስ አበባ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ቢሮ የሚከፈት ይሆናል፡፡ የጨረታ ሳጥኑ ከተዘጋ በኋላ የሚቀርብ የጨረታ መወዳደሪያ ሰነድ ተቀባይነት የለውም፡፡
- በጨረታው አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች ካሸነፉበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) የስራ ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን ገንዘብ ገቢ በማድረግ ንብረቱን መረከብ ይኖርባቸዋል፡፡ ይህ ካልሆነ ግን ያስያዙት ገንዘብ ለፋብሪካው ገቢ ሆኖ ከጨረታው ይሰረዛሉ።
- ፋብሪካው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ፡
አ.አ ማስተባበሪያ ስልክ ቁጥር 011 662 4656 አ/ቱሉ 0464419287 0917816996 (ንግድ መምሪያ) 0991659651 (ሽያጭ ቡድን) ፖ.ሣ.ቁ 1206 (አ.አ) 247 አ/ቱሉ
በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የአዳሚ ቱሉ የፀረ-ተባይ ማዘጋጃ ፋብሪካ
