የደራርቱ ቱሉ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በ2018 ዓ.ም አገልግሎት ላይ የሚውሉ የተለያዩ እቃዎችን ማለትም፡- ቋሚ እቃዎችን (6313) በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡-003/2015
የደራርቱ ቱሉ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በ2018 ዓ.ም አገልግሎት ላይ የሚውሉ የተለያዩ እቃዎችን ማለትም፡- ቋሚ እቃዎችን (6313) በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
በዚህ መሰረት ተጫራቾች፡-
- በመንግስት ዕቃ አቅራቢነት ተመዝግበው የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ እና ቫት ተመዝጋቢ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች በዘርፉ ወይም በመስኩ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው መሆን አለባቸው፡፡
- የዘመኑን ግብር የከፈሉና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ዘወትር በስራ ሰዓት በትምህርት ቤቱ ፋይናንስ ቢሮ ቁጥር 10 ብር 50.00 /ሀምሳ ብር/ በመክፈል የጨረታውን ሰነድ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ በገዙት ሰነድ ላይ ባለው የዋጋ ማቅረቢያ ቦታ በግልጽ በመሙላት በመጨረሻ ቦታ ላይ ስም፣ ፊርማና ህጋዊ ማህተም በማኖር በታሸገ ኤንቨሎፕ ዋናውን እና ፎቶ ኮፒውን በማሸግ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ዘወትር በስራ ሰዓት ከ2፡00-11፡00 ሰዓት ዋጋቸውን በመሙላት በተጠቀሰው የስራ ሰዓት የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ፡፡
- ለጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን የሚወዳደሩበትን ዋጋ በሲፒኦ ብር 2% (ሁለት ፐርሰንት) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ናሙና ለሚያስፈልጋቸው እቃዎች ጨረታው ሊዘጋ አንድ ቀን እስኪቀረው ድረስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታውን አሸናፊ ሆነው ከተገኙ በኋላ 10% ባሸነፉበት ዕቃ መጠን መሰረት የውል ማስከበሪያ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታውን ለማዛባት የሚሞክር ከጨረታው ውጪ እንደሚሆንና የጨረታውን ማስከበሪያ CPO እንደሚወረስባቸው ማወቅ አለባቸው፡፡
- ጨረታው የሚከፈተው ተጫራቾች እና ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታው በተዘጋ በቀጣዩ የስራ ቀን በ5፡00 ሰዓት በትምህርት ቤቱ ግዢ ንብረት አስተዳደር ጠቅላላ አገልግሎት ኬዝ ቲም ቢሮ ቁጥር 10 ይከፈታል፡፡
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡-011 434-7654/ 011-471-5349
አድራሻ፡- በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት ከቃሊቲ ቶታል ዝቅ ብሎ ከአሮጌው አስፓልት 200 ሜትር ገባ ብሎ
የደራርቱ ቱሉ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
