የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፑል ለ2018 በጀት ዓመት ለ2ኛ ዙር ከዚህ በታች ለተዘረዘሩት እቃዎች እና አገልግሎቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ግዥዎችን መፈፀም ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ የጨረታ ቁጥር 002/2018
የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፑል ለ2018 በጀት ዓመት ለ2ኛ ዙር ከዚህ በታች ለተዘረዘሩት እቃዎች እና አገልግሎቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ግዥዎችን መፈፀም ይፈልጋል፡፡
- ሎት 1 የቄብ ዶሮ፡-የጨረታ ማስከበሪያ ብር 30,000 /ሰላሳ ሺህ ብር ብቻ/
- ሎት 2 የዶሮ ኬጅ፡- የጨረታ ማስከበሪያ ብር 10,000 /አስር ሺህ ብር ብቻ/
- ሎት 3 የዶሮ መኖ:- የጨረታ ማስከበሪያ ብር 10,000 /አስር ሺህ ብር ብቻ/
- ሎት 4 የቢሮ የመስተንግዶ አገልግሎት ፡ የጨረታ ማስከበሪያ ብር 10,000.00 /አስር ሺህ ብር ብቻ/
በዚህም መሰረት፡- በጨረታው ለመወዳደር ፍላጎት ያላቸው የተጠቀሰውን መስፈርቶች የሚያሟላ ድርጅቶች እና ግለሰቦች በጨረታው እንዲሳተፉ ይጋበዛሉ፡፡
በዚሁ መሰረት ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ሆኔታዎች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት በልደታ የክ/ከተማ አስተዳደር ቅጥር ግቢ 9ኛ ፎቅ ክፍያና ሂሳብ ቡድን ቢሮ ቁጥር 901 በመቅረብ የማይመለስ ብር 300.00 /ሶስት መቶ ብር ብቻ/ በጥሬ ገንዘብ በመከፈል የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይቻላሉ፡፡
- ተጫራቾች፡-
ሀ. በዘርፉ ህጋዊ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያለው እና በመንግሥት ግዢ ኤጀንሲ /በሚመለከተው አካል /በአቅራቢነት የተመዘገበ
ለ. በተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገበ እና ቲን ነምበር ማቅረብ የሚችል፡፡
- በየሎቱ በተቀመጠው መሰረት የጨረታ ማስከበሪያ የብር መጠን CPO የልደታ ክ/ከ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አስተዳደርና ፋይናንስ ጽ/ቤት በሚል ስም በማሠራት ከሰነዱ ጋር ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከገዙ በኋላ የሚወዳደሩበትን ዋጋ በጨረታ ሰነድ ውስጥ በሚገኘው የዋጋ ማቅረቢያ ላይ በመሙላት በታሸገ ኤንቨሎፕ ለእያንዳንዱ ሎት ፋይናንሻል ኦሪጂናል እና ኮፒ ለየብቻ ቴክኒካል ኦርጂናልና ኮፒ ለየብቻ የድርጅቱን ክብ ማህተም በማድርግ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 /አስር/ ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ በልደታ የክ/ከተማ አስተዳደር ቅጥር ግቢ 9ኛ ፎቅ በሚገኘው የመንግሥት ግገዢ አስተዳደር ቡድን የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
- ለጨረታ ከቀረቡት ዕቃዎች ዝርዝር ውስጥ ጽ/ቤቱ እስከ 20% ጨምሮ ወይም ቀንሶ የመግዛት መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
- የጨረታ አሸናፊ ድርጅት ያሸነፈበትን ንብረት በራሱ ትራንስፖርት በልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር በዋና ሥራ አስፈጻሚ ህንፃ ግራወንድ ስር በሚገኘው የንብረት አስተዳደር ጠቅ/አገ/ቡድን ዕቃ ግምጃ ቤት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በወጣ በ11ኛው የሥራ ቀን 3፡00 ሰዓት ተዘግቶ የጨረታው ሳጥን በዕለቱ በ3፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር በዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት የመንግሥት ግዢ አስተዳደር ቡድን ቢሮ ውስጥ ይከፈታል። የጨረታው መክፈቻና መዝጊያ ቀን የሥራ ቀን ካልዋለ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ከላይበተጠቀሰው ተመሳሳይ ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ለሚወዳደሩበት ሎት 4 ዕቃዎች ናሙና ማቅረብ አለባቸው። ናሙና ለማይቀርብባቸው የዕቃ አይነቶች እና አገልግሎት ከመስሪያ ቤታችን በቀረበው ስፔስፊኬሽን መስፈርት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት ዕቃ ዋጋ ከነቫቱ መፃፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ከነቫቱ ያለመፃፍ ቫት እንዳለው ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ እንዲሁም የዘገየ ጨረታ እና በጨረታ መክፈቻ ላይ ያልተነበበ ፅሁፍ የጨረታው ሰነድ ተቀባይነት የለውም፡፡
- ጽ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- ልደታ ኮንዶሚኒየም በላይ ተክሱ ኬክ ቤት ጎን ወይም ተስፋ ኮኮብ ት/ቤት ከፍ ብሎ ልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በዋና ሥራ አስፈጻሚ ፑል የአስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት የመንግሥት ግዢ አስተዳደር ቡድን 9ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 901
ስልክ ቁጥር 251115153803
የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፑል
