ሲዳማ ብሮድካስትንግ ኮርፖሬሽን በ2018 በጀት ዓመት በሲዳሚኛ ቋንቋ በሲዳማ ቴሌቪዥን የሚተላለፍ ተከታታይ ክፍሎች ያሉትን አዝናኝና አስተማሪ ተከታታይ የቴሌቪዥን ስትኮም ድራማ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
ሲዳማ ብሮድካስትንግ ኮርፖሬሽን በ2018 በጀት ዓመት በሲዳሚኛ ቋንቋ በሲዳማ ቴሌቪዥን የሚተላለፍ ተከታታይ ክፍሎች ያሉትን አዝናኝና አስተማሪ ተከታታይ የቴሌቪዥን ስትኮም ድራማ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በመሆኑም በዚህ ጨረታ መወዳደር የሚችሉ፡-
- በዚህ ሙያ ዘርፍ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው
- ህጋዊ የንግድ ምዝግገባ ፍቃድ ያላቸው
- በመስኩ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው
- የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ያላቸው
- የቫት ተመዝጋቢነት ሰርተፍኬት ያላቸው ሀዋሳ ወንዶ ንግድ ኩባንያ ህንጻ ጀርባ በሚገኘው በኮርፖሬሽኑ ህንጻ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 202 በአካል መምጣት የተዘጋጀውን የጨረታ መመሪያ ሰነድ የማይመለስ ብር 200 በመክፈል መግዛት ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ 5,000 ብር በባንክ በተረጋገጠ CPO ብቻ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።
- ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ10 ተከታታይ ሥራ ቀናት ውስጥ የመወዳደሪያ ፕሮፖዛላችሁን ቴክኒካል ኦርጅናልና አንድ ኮፒ እንድሁም ፋይናንሻል ኦርጅናልና አንድ ኮፒ እያንዳንዳቸውን ለየብቻ በሰም በታሸገ ኤንቬሎፕ በማድረግ በአንድ ትልቅ ፖስታ በማሸግ ለዚህ በተዘጋጀ ጨረታ ሳጥን ማስገባት አለባቸው።
- ጨረታውም በ11ኛው ቀን ከቀኑ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በ4፡30 ሰዓት የሚከፈት ሲሆን ቀኑ የዕረፍት ቀን ወይም የበዓል ቀን ሲሆን በቀጣዩ ቀን በተመሳሳይ ቦታና ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- መሥሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፍልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 09 16 03 72 61 ደውሎ መጠየቅ የሚቻል መሆኑን እንገልጻለን።
ሲዳማ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን
