የጋሞ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በ2018 በጀት ዓመት 1- የተማሪ መማሪያ መጽሐፍ 2- ኖራ ውህድ ከነትራንስፖርቱ 3- የእንስሳት መድኃኒት 4- ፖሊቲን ቲውብ ባግ 5- ማጣቀሻ መጽሐፍት 6- የልብስ ስፌት ማሽን 7- የመበየጃ ማሽን 8. ለአካል ጉዳተኞች መርጃ መሣሪያ 9. የግንባታ ዕቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጋሞ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በ2018 በጀት ዓመት 1- የተማሪ መማሪያ መጽሐፍ 2- ኖራ ውህድ ከነትራንስፖርቱ 3- የእንስሳት መድኃኒት 4- ፖሊቲን ቲውብ ባግ 5- ማጣቀሻ መጽሐፍት 6- የልብስ ስፌት ማሽን 7- የመበየጃ ማሽን 8. ለአካል ጉዳተኞች መርጃ መሣሪያ 9. የግንባታ ዕቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም በጨረታው ለመሣተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች በተገለፀው መሠረት ቀርበው መወዳደር ይችላሉ፡፡
- በዘርፉ ሕጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸውና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤
- የዘመኑ ግብር የከፈሉበትን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤
- የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ያላቸውና በአቅራቢት የተመዘገቡ
- የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ ከፋይ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሣተፍ ከላይ በተራ ቁጥር ከ1-4 የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶች ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን አንስቶ እስከ 15 ባሉት ቀናት ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በጋሞ ዞን ፋይናንስ መምሪያ የባንክ ሂሣብ ቁጥር 1000038613263 በማስገባት እና የባንክ አድቫይስ ይዘው ከጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ ደረሰኙን በማሳየት ከጋሞ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ቢሮ ቁጥር 5 የጨረታ ሰነድ መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ተ. ቁ 1 የተማሪ መማሪያ መጽሐፍት 200,000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ ከተራ ቁጥር ከ2-9 ድረስ ያሉትን ለእያንዳንዱ 50,000 /ሃምሣ ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /CPO/ ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን በማዘጋጀት በፖስታ በጥንቃቄ በማሸግ የሚወዳደሩበትን ዓይነት በፖስታው ላይ በመለየት በግዥና ን/አስ/ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 5 በተዘጋጀው ሣጥን ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛው ቀን እስከ 3፡30 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ማስታወቂያው ከወጣበት እስከ 16ኛው ቀን በ3፡30 ሰዓት ታሽጐ በዕለቱ 4፡00 ሰዓት ቢሮ ቁጥር 5 ይከፈታል፡፡
- ማንኛውም ተጫራች ያሸነፈበትን ዕቃ ያለተጨማሪ ወጪ እስከ ቢሮአችን በማምጣት የማስረከብ ኃላፊነት አለበት፡፡
- የጨረታ መክፈቻ በበዓላት ወይም በሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይሆናል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 5 በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር-046-881-3338/046-881-0275 በመደወል መረጃዎችን ማግኘት ይችላሉ፡፡
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የጋሞ ዞን ፋይናንስ መምሪያ
አ/ምንጭ
