መዝዘዝ ንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ ከዚህ በታች በሎት የተዘረዘሩትን አቅርቦት ከአምራች ወይም አቅራቢ ድርጅቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
መዝዘዝ ንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ ከዚህ በታች በሎት የተዘረዘሩትን አቅርቦት ከአምራች ወይም አቅራቢ ድርጅቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
- በመሆኑም ከዚህ በታች በሎት ለተዘረዘሩት ጨረታዎች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ከታወቀ ባንክ የሚሰጥ ሲፒኦ ለእያንዳንዱ ሎት ከዚህ በሰንጠረዥ በተገለፀው የገንዘብ መጠን በመገዘዝ ንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ ስም በማሰራት ከዋናው የዋጋ ሰነድ ጋር አያይዘው ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
|
ተ.ቁ |
ሎት |
የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ |
|
1 |
ሎት አንድ፡ ድፍን ምስር |
100,000.00 |
|
2 |
ሎት ሁለት፡ የውጭ ሩዝ |
100,000.00 |
|
3 |
ሎት ሶስት፡ ዛላ በርበሬ |
100,000.00 |
|
4 |
ሎት አራት፡-በቆሎ |
100,000.00 |
|
5 |
ሎት አምስት፡-የዳቦ ዱቄት |
100,000.00 |
|
6 |
ሎት ስድስት፡-የእንሰሳት መኖ ማቀነባበሪያ ግብዓቶች (ፍሩሽካ፣ ፋጉሎ ፣ ጨው ፣ ሞላሰስ ፣ ኖራ…ወዘተ) |
100,000.00 |
- ተጫራቾች የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ሰርተፍኬት ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፍኬት፣ የዘመኑን ግብር መክፈላቸውን የሚያረጋግጥ ከግብር ሰብሳቢው ባለስልጣን የተሠጠ የምስክር ወረቀት እና ይቻላል፡፡ አቅራቢዎች አምራች ወይም ኤጀንት ከሆኑ በጨረታ ሰነዱ የተጠቀሱ ምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ዘወትር በስራ ሠዓት እስከ ቀኑ አስር ሠዓት ድረስ የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ከመዘዝ ንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ ግዥ ቡድን ቢሮ መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሃሣባቸውን የያዘ የዋጋ ሰነድ ዋናና ቅጅ ለየብቻው በታሸገ ኤንቨሎፕ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ ቀናት እስከ 15ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ በኢንተርፕራይዙ ቢሮ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው እንዲሁም ጨረታውን መታዘብ የሚፈልግ ማንኛውም አካል በተገኙበት ማስታወቂያው በወጣ በ15ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ታሽጎ 4፡30 በኢንተርፕራይዙ ግዥ ቡድን ቢሮ በግልፅ ይከፈታል፡፡ የመክፈቻው ቀን በሳምንቱ የዕረፍት ቀናት ወይም በዓል ላይ ከዋለ በሚቀጥለው የስራ ቀን ከላይ በተገለፀው ሰዓትና ቦታ በግልፅ ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች በሌላ ተጫራች ዋጋ ላይ ተመስርተው የመወዳደሪያ ዋጋ ማቅረብ አይችሉም፡፡
- የጨረታው ውጤት ለአሸናፊና ለተሸናፊ ተጫራቾች በእኩል ጊዜ በውስጥ ማስታወቂያ እና በደብዳቤ ይገለፃል፡፡
- ኢንተርፕራይዙ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥራችን /+251912211682/ ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
በደ/ብርሃን ዩንቨርሲቲ መገዘዝ ንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ
