የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ለሎት እንድ (Lot-1) የተማሪዎች ማደሪያ ማስፋፊያና ተያያዥ መገልገያዎችን እንዲሁም ለሎት ሁለት (lot-2 አዲስ ትምህርት ቤት ፕሮጀክት ግንባታ ማስተር ፕላንና ዲዛይን ክለሳ፣ የግንባታ ቁጥጥር እና የኮንትራት አስተዳደር የምክር አገልግሎት የሚሰሩ ደረጃ አንድ የማማከር ፍቃድ ያላቸውን ተጫራቾች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡
በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር: - SSNT-T585
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ለሎት እንድ (Lot-1) የተማሪዎች ማደሪያ ማስፋፊያና ተያያዥ መገልገያዎችን እንዲሁም ለሎት ሁለት (lot-2 አዲስ ትምህርት ቤት ፕሮጀክት ግንባታ ማስተር ፕላንና ዲዛይን ክለሳ፣ የግንባታ ቁጥጥር እና የኮንትራት አስተዳደር የምክር አገልግሎት የሚሰሩ ደረጃ አንድ የማማከር ፍቃድ ያላቸውን ተጫራቾች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡
ፕሮጀክቱን የማጠናቀቂያ ጊዜ ሥራው ከተጀመረበት በ450 ቀናት ውስጥ ለሎት አንድ (Lot -1) እና ለሎት ሁለት (Lot-2) ይሆናል።
ስለዚህ ከዚህ በታች የተገለጹትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች በጨረታው ላይ መሳተፍ ይችላሉ፡-
- ተጫራቹ ለ2017 ዓ. ም የታደስ ህጋዊ የንግድ ሥራ ፈቃድ ያለው ፣ የግብር ከፋይ ምዝገባ ሰርተፍኬት (TIN NO.) ማቅረብ የሚችል እና የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ የሆነ በጨረታዉ መሳተፍ ይችላል፡፡
- በዘርፉ ለመሰማራት የሚያስችል የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ፍቃድ ከሚሰጥ ህጋዊ አካል ለ2017 ዓ.ም የታደሰ ደረጃ አንድ ህንፃ ሥራ ተቋራጭ የማማከር ፍቃድ እና የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችል፣
- የዘመኑን ግብር የከፈለ እና ከታክስ ከእዳ ነጻ ስለመሆኑ ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችል፣
- የመንግስት መስሪያ ቤቶች በሚያወጡት ጨረታ ውስጥ ለመሳተፍ ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የተሰጠ ጊዜው ያላለፈበት የምዝገባ ወረቀት ማቅረብ የሚችል፣
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ይህ የጨረታ በማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ሰላሳ (30) ተከታታይ የሥራ ቀናት በአቅራቢያቸው ከሚገኝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ የማይመለስ አንድ መቶ ብር (100) በሂሳብ ቁጥር 1000006958277(E-99) ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ጨረታ ቁጥር SSNT-T585 በሚል ገቢ በማድረግና የከፈሉበትን የገቢ ደረሰኝ ኮፒ (Deposit Slip Copy) ቅጂውን (scan copy) በማድረግ ከታች በተጠቀሰው የኢሜይል አድራሻ በመላክ የጨረታ ሰነዱን ማግኘት ይችላሉ።
- በጨረታው የሚካፈል ማንኛውም ተጫራች ለሚጫረችበት ሁለት መቶ ሺህ ብር (200,000.00 ብር) የጨረታ ማስከበሪያ (Bid Bond) በባንክ በተረጋገጠ ሲ.ፒ.አ (C.P.O) ወይም ቅድመ ሁኔታ የሌለው የባንክ ዋስትና (unconditional Bank Guarantee) በኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ስም ማስያዝ አለባቸው። ከማንኛውም ኢንሹራንስ እና ቅድመ ሁኔታ ያለው (Conditional) የሚቀርብ ዋስትና ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
ተጫራቾች በጨረታው ደንብ መሰረት የመጨረቻ ሠነዳቸውን (ቴክኒካልና ፋይናንሻል) ዋናውን እና ኮፒውን በሰም በታሸነ ኤንቨሎፕ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ስትራቴጂክ ሶርሲንግ ክፍል እስከ ታህሳስ 01 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ሰዓት ድረስ ማቅረብ አለባቸው፡፡ ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት አዲስ አበባ ቦሌ በሚገኘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና መስሪያ ቤት ስትራቴጂክ ሶርሲንግ ነን ቴክኒካል የጨረታ መክፈቻ ክፍል በተመሳሳይ ቀን ከቀኑ 9:30 ሰዓት ይከፈታል።
ለተጨማሪ ማብራሪያ፦
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ
ቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ዋና መስሪያ ቤት
ስትራቴጂክ ሶርሲንግ ነን ቴክኒካል ክፍል
አቶ አሊ አስፋው
ስልክ ቁጥር: 011-517-4552
ኢ-ሜይል: AliAs@ethiopianairlines.com
አየር መንገዱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
