የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ በጨረታ ቁጥር አ.ሚ.ኔ.በ.ግ.ጨ. 008/2018ዓ.ም በግልፅ ጨረታ ሎት 1 የሬዲዮና የቴሌቪዥን ስቱዲዩ አኮስቲክስ ሥራ ግዥ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ በጨረታ ቁጥር አ.ሚ.ኔ.በ.ግ.ጨ. 008/2018ዓ.ም በግልፅ ጨረታ ሎት 1 የሬዲዮና የቴሌቪዥን ስቱዲዩ አኮስቲክስ ሥራ ግዥ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለመግዛት የሚፈልግ በመሆኑ በጨረታ ለመሳተፍ የምትፈልጉ፡-
- በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣
- የተጨማሪ እሴት ታክስ እና የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር የምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉና በግዥ አቅራቢነት የተመዘገቡ፣
- ተጫራቾች በሚያቀርቡት እያንዳንዱ ሰነድ እና በፖስታ ላይ የድርጅቱን ማህተምና ፊርማቸውን ማኖር ይጠበቅባቸዋል፡፡ ተጫራቾች ለሚያቀርቡት አጠቃላይ ዋጋ ለሎት1, 400.000 ብር በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር የሚያሳይ የጨረታ ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 10 የሥራ ቀናት ውስጥ አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ቢሮ ቁጥር 28 ሁለተኛ ፎቅ ለሰነዱ ከፍያ 300.00 (ሶስት መቶ ብር) በመክፍል ዘወትር በሥራ ሰዓት ቢሮ ቁጥር 6 ሰነዱን መውስድ ይችላሉ፡፡
- ጨረታው በ11ኛው ቀን ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከረፋዱ 4፡30 ተጫራቾች/ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ 8ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 108 ይከፈታል ፡፡ ሆኖም ግን የተጫራቾች አለመገኘት ጨረታውን ለመከፈት አያግደውም፡፡ የመክፈቻው ዕለት በዓል/ዕረፍት ቀን ከሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ተዘግቶ ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሃሳባቸውን ዋናውንና ኮፒውን /ቴክኒካል ኦሪጅናልና ኮፒ፣ ፋይናንሻል አሪጂናልና ኮፒ/በተለያየ ፖስታ በማሸግ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል፡፡
- በአንዱ ተጫራች ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ የተከለከለ ነው።
- በጨረታ ያሸነፈ ተጫራች ከመ/ቤታችን ጋር ጨረታውን እንዳሸነፈ ካወቀበት ጊዜ አንስቶ በ15 ቀናት ውስጥ በሲፒኦ የጠቅላላ ዋጋውን 10 % በማስያዝ ውል መዋዋል ይኖርበታል፡፡
- ተቋሙ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ፡- የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ 5 ኪሎ ቅድስት ማርያም ቤ/ክርስቲያን ከማህበረ ቅዱሳን ጀርባ ያለው ህንፃ።
ለበለጠ መረጃ ስልክ 0111116382 መደወል ይችላሉ፡፡
አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ
