ሕዳሴ ቴሌኮም አክሲዮን ማህበር የካፒታል ማርኬት የህግ አማካሪ ቅጥር አገልግሎት ግዥ ግልፅ ጨረታ (For Hiring a Legal Advisor for Transaction Advisory Services) በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
(For Hiring a Legal Advisor for Transaction Advisory Services)
ጨረታ ቁጥር LT/HT/HO/15/2025, ሕዳሴ ቴሌኮም አ.ማ
- ሕዳሴ ቴሌኮም አክሲዮን ማህበር የካፒታል ማርኬት የህግ አማካሪ ቅጥር አገልግሎት ግዥ ግልፅ ጨረታ (For Hiring a Legal Advisor for Transaction Advisory Services) በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከኅዳር 24 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ - እስከ ታኅሣሥ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ዘወትር በሥራ ሰዓት ከጠዋቱ 2፡30-6፡00 እንዲሁም ከሰዓት በኋላ ከ7፡30-10:00 ድረስ ቅዳሜ ጠዋት 2:30 እስከ 5:00 “ሕዳሴ ቴሌኮም አ.ማ" ደብረዘይት መንገድ ጠመንጃ ያዥ ባንክ አጠገብ ቴሌ ጋራዥ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 211 በመቅረብ የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ/ በመክፈል እና የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የታክስ ክሊራንስ ስርተፍኬት፣ እና የቫት ምዝገባ ሰርተፍኬት ፎቶኮፒውን በመያዝ የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የሚያቀርቡት
- አንድ ዋና /Original/ የጨረታ ሰነድ ለብቻው በስም በታሸገ ፖስታ ታሽጐ፣
- አንድ ቅጂ /Copy/ የጨረታ ሰነድ ለየብቻው በሰም በታሸገ ፖስታ ታሽጐ እንዲሁም፣
- ሁሉም በአንድ ላይ በትልቅ ፖስታ ውስጥ ተካቶ በሰም የታሸገ መሆን አለበት።
- በዋናውና በቅጂው መካከል ልዩነት ቢፈጠር ዋናው ተቀባይነት ይኖረዋል። ተጫራቾች የሚያቀርቡት የጨረታ ሰነድ ላይ ስርዝ ድልዝ መኖር የለበትም። የተሰረዘ ሰነድ በፊርማ መረጋገጥ ይኖርበታል።
- ተጫራቾች የሚያቀርቡበትን የጨረታ ማስከበሪያ ብር 10,000.00 (አስር ሺህ) የባንክ ክፍያ ማዘዣ /C.P.O/ ብቻ ለሕዳሴ ቴሌኮም አ.ማ በሚል ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ያዘጋጁትን የጨረታ ሰነድ እስከ ታኅሣሥ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ቢሮ ቁጥር 211 ማስገባት ይችላሉ፣ ጨረታው በዚሁ እለት ታኅሣሥ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ቢሮ ቁጥር 211 የሚከፈት ይሆናል።
ከላይ የተገለጸውን መመሪያ ያልከተሉ ተጫራቾች ወዲያውኑ ከጨረታ ውድድሩ የሚሰረዙ መሆኑን እንገልጻለን።
ተጫራቾች ተጨማሪ መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 0978230511-0968271291 መጠቀም ይችላሉ።
- ሕዳሴ ቴሌኮም አ.ማ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ሕዳሴ ቴሌኮም አክሲዮን ማህበር
