ገነት ሆቴል የጥራት ደረጃቸውን የጠበቁ የበሬ እና የበግ ተዋፅኦ የዶሮ እና የአሳ ተዋፅኦ እንዲሁም የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችን አወዳድሮ አብሮ መስራት ይፈልጋል።
ስጋ፣ የዶሮ፣ የአሳ እና የአትክልትና ፍራፍሬ
የጨረታ ማስታወቂያ
ገነት ሆቴል የጥራት ደረጃቸውን የጠበቁ የበሬ እና የበግ ተዋፅኦ የዶሮ እና የአሳ ተዋፅኦ እንዲሁም የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችን አወዳድሮ አብሮ መስራት ይፈልጋል። ስለሆነም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ቅድመ መስፈርቶች ማሟላት የሚችሉ ድርጅቶች መወዳደር ይችላሉ።
-
- የ2018 ዓ.ም ዘመን የታደሰ የንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚችሉ፤
- የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ሰርተፍኬት (VAT) ያላቸው፤
- የግብር ከፋይ ምዝገባና ሰርተፍኬት መለያ ቁጥር ሰነድ ያላቸው፤
- በጨረታ መሳተፍ የሚያስችል የታክስ ክሊራንስ ማቅረብ የሚችሉ፤
- ከዚህ ቀደም ከድርጅቱ ጋር የውል ስምምነት ኖሮት የመልካም ስራ አፈፃፀም / የአቅርቦት ችግር የሌለበት ፤
- ተጫራቾች ስለጨረታው ሙሉ ዝርዝር ሁኔታ የያዘውን የጨረታ ሰነድ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ታሳቢ የሚደርግ 10 (አስር) ተከታታይ ቀናት ጊዜ ውስጥ ከድርጅታችን የፋይናንስ ቢሮ ክፍል የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 300 (ሶስት መቶ ብር) ከፍለው መውሰድ ይጠበቅባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 5,000.00 (አምስት ሺህ) ብር በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ለ “ገነት ሆቴል” በሚል በማሰራት ከቴክኒካል ሰነድ ጋር ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
- ተጫራቾች የቴክኒካል ሰነድ እና ፋይናንሻል ሰነድ በተናጥል ለየብቻ በፖስታ በማሸግ እስከ አስረኛ ቀን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ በድርጅቱ አስተዳደር ክፍል ለዚሁ አገልግሎት በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት ይጠበቅባቸዋል ፤ አስረኛ ቀን የስራ ቀን ካልሆነ የጨረታው መክፈቻ በቀጣይ ባለው ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይሆናል።
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ተወካዮች ባሉበት በአስረኛው ቀን ከቀኑ 8፡30 በድርጅቱ አዳራሽ ይከፈታል።
- ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- አ/አ በሜክሲኮ ወደ ቄራ በሚወስደው መንገድ
ለተጨማሪ ማብራሪያ፡- 0115-50-47-01/ 0939-500000
ገነት ሆቴል
