በሲዳማ ብሔራዊ ከልላዊ መንግሥት የማልጋ ወረዳ ፋይ/ኢኮ/ል/ጽ/ቤት በኩል በወረዳው መንገድና ትራንስፖርት በ2018 በጀት ዓመት ሊሰራ ካቀደው መሰረተ ልማት ለተለያዩ ለወረዳው ቀበሌያት መንገድ ሥራ የሚሆን ሰሌክት /SELECT/ ጠጠር በግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በሲዳማ ብሔራዊ ከልላዊ መንግሥት የማልጋ ወረዳ ፋይ/ኢኮ/ል/ጽ/ቤት በኩል በወረዳው መንገድና ትራንስፖርት በ2018 በጀት ዓመት ሊሰራ ካቀደው መሰረተ ልማት ለተለያዩ ለወረዳው ቀበሌያት መንገድ ሥራ የሚሆን ሰሌክት /SELECT/ ጠጠር በግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በዚህ መሰረት፡-
- የታደሰ የንግድ ሥራ ፍቃድ ያላቸው: የዘመኑን ግብር የከፈሉ፡ ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ፡ አቅራቢነት ምዝገባ ምስክር ወረቀት ያላቸውና የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ
- በግንባታ አፈጻጸም ችግር ምክንያት ማስጠንቀቂያ የተሰጠው ተጫራች ጨረታውን መወዳደር አይችልም።
- ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ለ15 (አስራ አምስት) ተከታታይ ቀናት በአየር ላይ የሚውል ይሆናል።
- ተጫራቾች ዋጋ የተሞላበትን 1 /አንድ/ ኦርጅናልና 1 /አንድ/ ፎቶ ኮፒ የጨረታ ሰነድና የጨረታ ማስከበሪያ CPO 20,000 /ሀያ ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ ዋስትና በፖስታ ለየብቻቸው በማሸግ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን አንስቶ ለ15 ተከታታይ ቀናት የማይመለስ ብር 300 /ሶስት መቶ ብር/ በማ/ወ/ፋይ/ በግዥ የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 14 በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
- ይህ ጨረታ በ16ኛው ቀን ከ5፡00 – 6፡00 ሰዓት ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ሰነዳቸውን በሰም አሽገው ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው በዚሁ ቀን ከቀኑ 8፡00 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- የተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው አለመገኘታቸው ጨረታውን ከመክፈት አያግደውም።
- የጨረታ አሸናፊው የጨረታ ውጤት ሲታወቅ የውል ማስከበሪያ ከጠቅላላ የጨረታ ዋጋ 10% CPO /Bid Bond/bid security/ በባንክ በተረጋገጠ ዋስትና ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው የሚከፈትበት የሥራ ቀን ላይ ካልዋለ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተገለጸው ቦታና ሰዓት የሚከፈት ይሆናል።
ማሳሰቢያ፡- አሰሪው መ/ቤት የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ ለሙሉ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የማልጋ ወረዳ ፋይ/ኢኮ/ል/ጽ/ቤት
