ሰላም የህዝብ ማመላለሻ አ/ማ ያገለገሉ የዩቶንግ አውቶቢሶችን በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ያስችለው ዘንድ ተሽከርካሪዎቹ አሁን ላይ ያሉበትን ቴክኒካል ብቃት መነሻ በማድረግ የጨረታ መነሻ ዋጋ ትመና (ግምት) (Assete Valuation) ማስገመት ስለሚፈልግ በዘርፉ የተሰማሩ ባለሙያዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
ሰላም የህዝብ ማመላለሻ አ/ማ ያገለገሉ የዩቶንግ አውቶቢሶችን በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ያስችለው ዘንድ ተሽከርካሪዎቹ አሁን ላይ ያሉበትን ቴክኒካል ብቃት መነሻ በማድረግ የጨረታ መነሻ ዋጋ ትመና (ግምት) (Assete Valuation) ማስገመት ስለሚፈልግ በዘርፉ የተሰማሩ ባለሙያዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።
ስለሆነም፡- አ/ማህበሩ ያገለገሉ የዩቶንግ አውቶቢሶች ወቅታዊ ዋጋ ትመና (ግምት) (Asset Valuation) ለማስገመት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ስለሚፈልግ በጨረታው መወዳደር ለሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች ከዚህ በታች በተገለፀው የጨረታ መመሪያ መሠረት መሳተፍ ይችላል።
- ተጫራቾች በዘርፉ የተሰማሩ ሕጋዊ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው የምዝገባ የምስክር ወረቀት የዘመኑን ግብር የከፈሉና ክሊራንስ የተሰጣተቸዉ የተጨማሪ እሴት ታክስ የምስክር ወረቀት እና TIN ቲን ሰርቲፊኬት ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በሪፖርተር ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከሰኞ እስከ አርብ ዘወትር ከ2:30-11:00 ሰዓት እንዲሁም ቅዳሜ 2፡30-6:30 ሰዓት የማይመለስ ብር 300.00 (ሶስት መቶ) በመክፈል የንብረቶቹን ዝርዝር መረጃ የያዘ የተጫራቾች መመሪያ እና የዋጋ ማቅረቢያ ቅፅ በአ/ማህበሩ ዋና መ/ቤት መስቀል አደባባይ ፊንፊኔ ህንፃ 6ተኛ ፎቅ ማግኘት ይችላሉ።
- ተጫራቾች ለሚያቀርቡት ዋጋ የጨረታ ማስከበርያ (bid bond) የአጠቃላይ ዋጋዉን አምስት በመቶ (5%) በባንክ ክፍያ ማዘዣ በተረጋገጠ ቼክ ወይም ሲፒኦ (CPO) በሰላም የህዝብ ማመላለሻ አ/ማ (Selam bus line share company) ስም አሰርተዉ ማስገባት ይኖርቸዋል። ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ በድርጅቱ ጋራጅ ዉስጥ ለዚሁ በተዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ዉስጥ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል።
- ተጫራቾች ተሽከርካሪዎቹ በሚገኙባቸዉ የአ/ማህበሩ ጋራጆች በአካል ተገኝተዉ ያሉበትን ቴክኒካል ብቃት የመገምገም ግዴታ አለባቸዉ።
- ጨረታዉ ታህሳስ 27 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት በ9፡15 በድርጅቱ መሰብሰብያ አዳራሽ ይከፈታል።
- ማንኛዉም ተጫራች ቴክኒካል እና ፋይናንሽያል ፕሮፖዛሎች ለየብቻ በማዘጋጀትና በማሽግ ሁለቱንም ፕሮፖዛሎች በአንድ ኢንቨሎ በማሸግ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማቅረብ አለባቸዉ።
- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ።
- ተጫራቾች በሚከተለዉ የጨረታ ቀናት መሰረት መሳተፍ ይችላሉ።
|
ተ/ቁ |
የድርጅቱ ስም |
የጨረታው አይነትና ቁጥር |
ጨረታው የወጣበት ቀን |
የጨረታው መዝጊያና መክፈቻ ቀን |
|
1 |
ሰላም የህዝብ ማመላለሻ አ/ማ |
ያገለገሉ የዩቶንግ አዉቶቢሶች ወቅታዊ ዋጋ ትመና (ግምት) (Asset Valuation) ግልፅ ጨረታ ሰ/ህ/ማ/አ/ማ/003/2018
|
ታህሳስ 11 ቀን 2018 ዓ.ም |
ታህሳስ 30 ቀን 2018 ዓ.ም 9፡00 ተዘግቶ በእለቱ 9፡15 ቅ/ሚካኤል ግቢ ውስጥ በሚገኘው የአ/ማህበሩ መሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል። |
ለተጨማሪ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 09-47-34-62-00 // 011-470-83-32 ደውለው ይጠይቁ።
