የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የግንባታና የሕንፃ መሣሪያ ዕቃዎች እና የኤሌክትሪክ ዕቃዎች ለ2018 ዓ.ም እና ለ2019 ዓ.ም በጀት ዓመት በማዕቀፍ ግዥ በጨረታ መለያ ቁጥር ፌ.ቤ.ኮ/ማዕ 2018-2019/ዕግ/ብ.ግ.ጨ/33/04/2018 ተጫራቾችን አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡- ፌ.ቤ.ኮ/ማዕ 2018-2019 /ዕግ/ብ.ግ.ጨ 33/04/2018
- የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የግንባታና የሕንፃ መሣሪያ ዕቃዎች እና የኤሌክትሪክ ዕቃዎች ለ2018 ዓ.ም እና ለ2019 ዓ.ም በጀት ዓመት በማዕቀፍ ግዥ በጨረታ መለያ ቁጥር ፌ.ቤ.ኮ/ማዕ 2018-2019/ዕግ/ብ.ግ.ጨ/33/04/2018 ተጫራቾችን አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
- ለኮርፖሬሽኑ አገልግሎት የሚውል የግንባታና የሕንፃ መሣሪያ ዕቃዎች እና የኤልክትሪክ ዕቃዎች ግዥ ተጫራቾች የመወዳደሪያ ቴክኒካል ሰነዳቸውንና ዋጋቸውን በተለያዩ በታሸጉ ኢንቨሎፖች ማቅረብ አለባቸው።
- ጨረታው የሚከናወነው በብሔራዊ ግልጽ ጨረታ ሥነ ሥርዓትና ይህንኑ አስመልክቶ በፌዴራል መንግሥት ባለቤትነት የተያዙ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች የግዥ አፈፃፀም መመሪያ መሠረት ሲሆን ከሚፈለገው አገልግሎት ጋር የተዛመደ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የግብር ከፋይ ማስረጃ የሚያቀርቡ መሆን ይኖርበታል፡፡
- የተሟላ የጨረታ ሰነዶችን ማንኛውም ፍላጎት ያለው ተጫራች ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ30 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የማይመለስ ብር 300.00 /ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ለገሀር በሚገኘው የኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 209 በኮርፖሬሽኑ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በአካል በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዶቻቸውን በኮርፖሬሽኑ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 209/212 ለዚሁ ታሽጎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 30ኛው ቀን ወይም ጥር 18 ቀን 2018 ዓ.ም ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ እንዲያቀርቡ ሆኖ ተጫራቾች ለእያንዳንዱ ሎቶች ብር 30,000.00 ለሎት 1 የግንባታና የሕንፃ መሣሪያ እቃዎች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 30,000.00 (ሰላሳ ሺህ ብር) እንዲሁም ለሎት 2 የኤሌክትሪክ እቃዎች ብር 30,000.00 (ሰላሳ ሺህ ብር) በባንክ በተመሰከረለት ቼክ ወይም ሲፒኦ በፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ስም ከጨረታ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው:: ዘግይቶ የቀረበ የጨረታ ሰነድ ውድቅ ይደረጋል፤ ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ቀን ጥር 18 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከጠዋቱ 4፡15 ሰዓት የኮርፖሬሽኑ ግዥና ንብረት አስተደደር ዳይሬከተር 2ኛ ፎቅ ይከፈታል፡፡
- ኮርፖሬሽኑ በሚያወጣው ፕሮግራም መሠረት አሸናፊው ተጫራች አሸናፊ ሆነው የተመረጡባቸውን ዕቃዎች በራሳቸው ትራንስፖርት /ማጓጓዣ ኮርፖሬሽኑ ድረስ ያስረክባል፡፡
- ኮርፖሬሽኑ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር:- 011-515-77-28 ወይም 011-553-95-35 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን
