የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን ለ2018 በጀት ዓመት በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ለሚያከናውነው አስቸኳይ ፕሮጀክቶች ግብዓት የሚያገለግል የኮንክሬት ቱቦ (RC-Pipe 48 Ø and 420) ምርት በቁርጥ ዋጋ ከዚህ በታች የተቀመጡትን መስፈርቶች ከሚያሟሉ አቅራቢዎች መግዛት ይፈልጋል፡፡
የኮንክሬት ቱቦ (RC-PiPe 48 and 42 ዲያሜትር) ምርት የቁርጥ ዋጋ ግዥ ጥሪ ማስታወቂያ
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን ለ2018 በጀት ዓመት በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ለሚያከናውነው አስቸኳይ ፕሮጀክቶች ግብዓት የሚያገለግል የኮንክሬት ቱቦ (RC-Pipe 48 Ø and 420) ምርት በቁርጥ ዋጋ ከዚህ በታች የተቀመጡትን መስፈርቶች ከሚያሟሉ አቅራቢዎች መግዛት ይፈልጋል፡፡
|
ተ.ቁ |
የምርቱ ዓይነት |
መለኪያ |
ብዛት |
የአንድ ሜትር ነጠላ ዋጋ. ትራንስፖርት ተ.እ.ታ ጨምሮ |
|
1 |
የኮንክሬት ቱቦ (RC-Pipe 42 Ø ምርት |
ሜትር |
20,000 |
27,393.75 ብር |
|
2 |
የኮንክሬት ቱቦ (RC-Pipe 48 Ø ምርት |
ሜትር |
3,000 |
37,704.25 ብር |
1. አግባብነት ያለው ለዘመኑ የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ፣ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፍኬት፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ሰርተፍኬት እና የዘመኑን ግብር የከፈሉበትን ታክስ ክሊራንስ ኦርጅናልና ኮፒ ማቅረብ እንዲሁም በመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ድረ-ገጽ ላይ መመዝገብ ይኖርባቸዋል፡፡
2. የኮንክሪት ቱቦ ማምረቻ ማሽኑ ባለቤትነት ማረጋገጫ ወይም ሕጋዊ ውክልና እንዲሁም በሕግ አግባብነት ካለው አካል የተሰጠ ኮንክሪት ቱቦ ለማምረትና ለገበያ ለማቅረብ የሚያስችል ፍቃድ፣ ወይም ኮንክሪት ቱቦ ለማምረትና ለገበያ ለማቅረብ የሚያስችል ፍቃድ ካለው ግለሰብ/ማህበር የተሰጠ ሕጋዊ/በፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫ ጽ/ቤት የተረጋገጠ ውከልና አያይዞ ማቅረብ አለባቸው።
3. አቅራቢው ቢያንስ በቀን 100 ሜትር ባለ 2ሜትር እና ከዚያ በላይ ርዝመት ያለው የኮንክሪት ቱቦ አምርቶ ማቅረብ አለበት፡፡
4. የሚቀርበዉ ምርት በባለሥልጣን መ/ቤቱ የጥራት መመዘኛ መስፈርት /specification/ መሠረት መሆኑ መ/ቤቱ በላብራቶሪ የጥራት ፍተሻ ያከናወናል፡፡
5. አቅራቢዎች የኮንክሬት ቱቦ (RC-PiPe 48 Ø and 42 Ø) ምርት በሚሰጣቸው ድልድል መሠረት ወደ ፕሮጀክት ሳይት አጓጉዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
6. አቅራቢዎች ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ወይም በሬዲዮ ጥሪ ከተላለፈበት ቀን ጀምሮ በሥራ ቀን እና ሰዓት በባለሥልጣኑ ዋና መ/ቤት 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 23 ከላይ የተገለፁትን ማስረጃዎች ኦርጅናልና ኮፒ ይዘው በመቅረብ መመዝገብ ይኖርባቸዋል፡፡
ባለሥልጣን መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ የግዥ ፍላጎቱን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ ስ.ቁ 011-3-72-28-25/011-3-71-41-03
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን ሳርቤት ፑሽኪን አደባባይ አጠገብ
