የአርባ ምንጭ ከተማ ፋይናንስ እና ፕላን ልማት መምሪያ ለአ/ም/ከ/ማዘጋጃ ቤት የህንጻ መሳሪያ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የዕቃ ግዥ ጨረታ ጥሪ
የአርባ ምንጭ ከተማ ፋይናንስ እና ፕላን ልማት መምሪያ ለአ/ም/ከ/ማዘጋጃ ቤት -
1. የህንጻ መሳሪያ ግዥ ፡-
ከዚያ በላይ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ መስፈርቱን የምታሟሉ ተጫራቾች በጨረታው እንድትወዳደሩ ተጋብዛችኋል፡፡
1. በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፊቃድ ያላቸው የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ያላቸው የግብር ከፋይ ቁጥር (TIN No) ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ
2. አቅራቢነት ማስረጃ ማቅረብ የሚችል /online/
3. ከሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ ለእያንዳንዱ ጨረታ 20,000.00 /ሃያ ሺህ ብር/ በባንክ በተመሰከረ ሲፒኦ ከጨረታው ሰነድ ጋር አያይዞ ማቅረብ የሚችል፡፡
4. ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ለ15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ በአ/ም/ከ/ፋእና ፕላን ልማት መምሪያ ቢሮ ቁጥር 3 በመቅረብ የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሰነድ እንድትግዙ እንገልፃለን ፡፡
5. ዋጋቸውን በማያሻማ መልኩ እንድታቀርቡ እናሳውቃለን ፡፡
6. የጨረታ ሠነድ የሚገባው ጨረታው አየር ላይ ከዋለበት በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ነው።
7. የጨረታ ሣጥን የሚታሸገው በዕለቱ ከረፋዱ 4፡00 ሲሆን የሚከፈተው 4፡30 በከተማው በአ/ም/ከፋና ፕላን መምሪያ ይሆናል፡፡
8. ተጫራቾቹ ጨረታ ዶከምንት ቴክኒካልና ፋይናንሻል/ ኦርጅናልና ኮፒ እንዲሁም CPO በተለያዩ ፖስታ አድርው በእናት ፖስታ አሽገው እንዲያቀርቡ ይፈልጋል፡፡
9. ውል ማስከበሪያ ማስያዝ የሚችል፤
10. በሌላ ተጫራች ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይቻልም።
11. ተጫራቾች የውል ማስከበሪያ የውሉን 10% ማስያዝ የሚችሉ መሆኑ አለባቸው።
12. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብት አለው፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ:- 0468 81 23 89/0468 81 43 53/0468 81 46 19
በደቡብ ክልል በጋሞ ዞን አ/ም ከተማ ፋ/እና ፕላን ልማት መምሪያ
