በኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከደቡብ ምዕራብ አዲስ አበባ ዲስትሪክት በሊዝ ፋይናንሲንግ ሥርዓት መሠረት ለሚስማር ማምረቻ የሚውሉ ማሽነሪዎችን በዱቤ ኪራይ ወስደው የነበሩና ከዚህ በታች በስም የተጠቀሱ ግለሰብ በገቡት የዱቤ ግዢና ኪራይ ውል መሠረት ግዴታቸውን ባለመወጣታቸው ምክንያት ባንኩ መልሶ የተረከባቸው ማሽነሪዎችን ባሉበት ሁኔታ በጨረታ መሸጥ/ ማከራየት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
በኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከደቡብ ምዕራብ አዲስ አበባ ዲስትሪክት በሊዝ ፋይናንሲንግ ሥርዓት መሠረት ለሚስማር ማምረቻ የሚውሉ ማሽነሪዎችን በዱቤ ኪራይ ወስደው የነበሩና ከዚህ በታች በስም የተጠቀሱ ግለሰብ በገቡት የዱቤ ግዢና ኪራይ ውል መሠረት ግዴታቸውን ባለመወጣታቸው ምክንያት ባንኩ መልሶ የተረከባቸው ማሽነሪዎችን ባሉበት ሁኔታ በጨረታ መሸጥ/ ማከራየት ይፈልጋል።
|
ተ.ቁ |
የተከራይ ስም |
በጨረታ የሚሸጠው/የሚከራየው ንብረት የሚገኝበት ቦታ |
የንብረቱ ዝርዝር አይነት |
የጨረታው መነሻ ዋጋ (በብር) |
የጨረታው ደረጃ |
ጨረታው የሚካሄድበት ቀንና ሰዓት |
|
1 |
ያሬድ ሰይፈሚካኤል ሙሉጌታ |
አዲስ አበባ ከተማ፣ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ፣ ወረዳ 05፣ የቤት ቁጥር 472 የሆነ መጋዘን ውስጥ |
WIRE DRAWING & NAIL MAKING MACHINE. (የዕቃው ዝርዝር መረጃ ከጨረታ ሰነዱ ያገኛሉ) |
41,276,919.27 |
2ኛ ዙር ጨረታ |
ሚያዝያ 06 ቀን 2018 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00-6፡00 ሰዓት |
የሐራጁ መመሪያ፣
1. የጨረታ ሰነዱን በባንኩ ኮርፖሬት ቅርንጫፍ ዳይሬክቶሬት ቀርቦ የማይመለስ አንድ መቶ ብር (ብር 100.00) ክፍያ በመፈጸም መግዛት የሚችሉ ሲሆን፤ ከላይ የተመለከተውን ጉብረቶች ለመግዛት ወይም ለመከራየት በጨረታው መሳተፍ የሚፈልግ አካል (ግለሰቦች) ተቋማት ወይም አነስተኛና መካከለኛ ማህበራት) የሀራጁን የመነሻ ዋጋ 1/4ኛ (25 በመቶ) በባንክ የተረጋገጠ ሲ.ፒ.ኦ (CPO) በማስያዝ (በማቅረብ) መጫረት ይኖርበታል፣
2. ጨረታው ተጫቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከላይ በተጠቀሰው ቀገና ሰዓት ንብረቱ በሚገኝበት መጋዘን ቅጥር ግቢ ውስጥ ይካሄዳል፤
3. ንብረቱን ሙሉ በሙሉ በጥሬ ገንዘብ ለመግዛት ተወዳድሮ ያሸነፈ ተጫራች ቀሪውን ገንዘብ 15% ተ.እ.ታ (VAT) ጨምሮ በ15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ አጠቃሎ መክፈል ይኖርበታል። የጨረታው አሸናፊው በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ቀሪውን ገንዘብ አጠቃሎ ካልከፈለ ጨረታው ተሰርዞ ያስያዘው ገንዘብ በሙሉ ለባንኩ ገቢ ይደረጋል፤
4. ንብረቱን ሙሉ በሙሉ በጥሬ ገንዘብ ወይም እጅ በእጅ ሽያጭ ለመግዛት ተወዳድሮ ያሸነፈ ተጫራች ንብረቱን ከመረከቡ በፊት በዘርፉ ከቀረጥ ነጻ የመጠቀም መብት ማቅረብ ወይም መንግስት ከንብረቶቹ የሚፈለገውን የጉምሩክ ቀረጥ እና ታክስ መክፈል ግዴታ አለበት፤
5. በጨረታው መሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውም አካል የጨረታው አሸናፈ ከሆንና ንብረቱን በባንኩ ማሽነሪ ዱቤ ግዢ እና ኪራይ መሠረት የመከራየት ዕቅድ ካለው የባንኩን የማሽነሪ ኪራይ መስፈርት ስለማሟላቱ በቅድሚያ እርግጠኛ መሆን፤ እንዲሁም በባንኩ በሚከናወን የፕሮጀክት ጥናት ላይ የሚቀመጡ ቅድመ ሁኔታዎችን መስማማት ይጠበቅበታል።
6. አሸናፊው ተጫራች ንብረቱን በማሽነሪ ዱቤ ግዢ እና ኪራይ ውል ለመከራየት የሚፈልግ ከሆነ በባንኩ አሰራር መሠረት የሚጠበቅበትን ቅድሚያ ክፍያ በ15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ በመክፈል የባንኩን የማሽነሪ ዱቤ ግዥ እና ኪራይ መስፈርት በማሟላት ውል መፈረም ይኖርበታል። በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ግዴታውን ካልተወጣ የጨረታ አሸናፊነቱ ተሰርዞ ያስያዘው ገንዘብ በሙሉ ለባንኩ ገቢ ይሆናል።
7. በሐራጅ ለተሸነፉ ተጫራቾች ለሐራጅ ያስያዙት ገንዘብ (CPO) በባንኩ ማህተም ተረጋግጦ ይመለስላቸዋል፤
8. ስለ እያንዳንዱ ንብረት ዝርዝርና ተጨማሪ መረጃ (የጨረታ ሰነድ) ለማግኘት ክፍያ ከፈጸሙ በኋላ ሜክሲኮ አልሳም ጨለለቅ ህንጻ 2ተኛ ወለል ላይ በሚገኘው የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ደቡብ ምዕራብ አዲስ አበባ ዲስትሪክት ማነጋገር ወይም በስልክ ቁጥር +251-11-558-6175 ደውሎ ማነጋገር ይቻላል፤
9. ጉብረቶቹን ለመጎብኘት የሚፈልግ ከደቡብ ምዕራብ አዲስ አበባ ዲስትሪክት ጋር በመነጋገር አስቀድሞ ቀጠሮ በመያዝ ወይም በባንኩ መርሃግብር መሠረት ሚያዝያ 05 ቀን 2018, ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30-5፡30 ሰዓት መመልከት ይችላሉ።
10. ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፈል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ደቡብ ምዕራብ አዲስ አበባ ዲስትሪክት
