የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደደር የኮንስትራክሽን ዲዛይን፣ ግንባታና ማማከር ድርጅት የአርማታ ብረቶች ከ ባለ 8 እስከ ባለ 20 ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የአርማታ ብረቶች ግዥ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር የኮ/ዲ/ግ/ማ/ድ/ግ/ጨ/ቁ 18/2018
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደደር የኮንስትራክሽን ዲዛይን፣ ግንባታና ማማከር ድርጅት የአርማታ ብረቶች ከ ባለ 8 እስከ ባለ 20 ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ስለሆነም፡-
1. በጨረታው ለመካፈል የሚፈልጉ ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ የሚያስችል በዘርፉ የተሰጠ የታደሠ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፤ የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ኮፒ አያይዘው ማቅረብ የሚችሉ የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ መሆናቸውን ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ ድርጅቶችና ግለሰቦች የጨረታ ሠነድ የማይመለስ ብር 300.00 (ሦስት መቶ) ብር በመክፈል በአዲስ አበባ ከተማ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቃሊቲ ማሰልጠኛ ፊት ለፊት የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ቢሮ አጠገብ የኮንስትራክሽን ዲዛይን፣ ግንባታና ማማከር ድርጅት ቢሮ በመቅረብ የተዘጋጀውን የጨረታ ሠነድ መግዛት ይችላሉ።
2. ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት ግብአት በጨረታ ሠነዱ በተገለፀው መሠረት የፍተሻ ሰርተፍኬት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
3. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 300,000.00 /ሦስት መቶ ሺህ ብር/ ከታወቀ ባንክ የሚሰጥ በባንክ የተረጋገጠ ቼክ (ሲ.ፒ.ኦ) ወይም በሁኔታዎች ላይ ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና (unconditional bid bond guarantee) ከሚያቀርቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ጋር በማያያዝ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
4. ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለአሥር ተከታታይ ቀናት በአየር ላይ የሚቆይ ሆኖ በ11ኛው ቀን ከረፋድ 4፡30 ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከረፋዱ 5፡00 ተሳታፊዎች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
5. የኮንስትራክሽን ዲዛይን፣ ግንባታና ማማከር ድርጅት የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- በአዲስ አበባ ከተማ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቃሊቲ ማሰልጠኛ ፊት ለፊት የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ቢሮ አጠገብ።
ስልክ ቁጥር፡- 09 13-56-49-36/ 09 11-15-60-36
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮንስትራክሽን ዲዛይንና ግንባታና ማማከር ድርጅት
