Tender Detail

Tender Details

  • Company የደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት
  • Address ሀዋሳ ከተማ ፡ ሲዳማ ክልል ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 046-2-20-59-92
  • Website
  • Deadline13 May 2026, 12:00 AM
  • magazineአዲስ ዘመን
  • Bid Document Price400.00
  • opening date2026-05-13 00:00:00
  • Categories Food And Beverage

የደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት በሀዋሳ እና በሆሳዕና በድርጅቱ መጋዘኖች ተከማችቶ የሚገኝ በአሶሳ አካባቢ የተመረተ ከዘርነት የተረፈ ለምግብነት የሚውል ንፁህ የበቆሉ እህል ለሁለተኛ ጊዜ እንዲሁም ንጹህ የስንዴ እህል ለመጀመሪያ ጊዜ በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።


የጨረታ ማስታወቂያ የጨረታ

ቁጥር 009/ሽያጭ/18 .

 

የደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት በሀዋሳ እና በሆሳዕና በድርጅቱ መጋዘኖች ተከማችቶ የሚገኝ በአሶሳ አካባቢ የተመረተ ከዘርነት የተረፈ ለምግብነት የሚውል ንፁህ የበቆሉ እህል ለሁለተኛ ጊዜ እንዲሁም ንጹህ የስንዴ እህል ለመጀመሪያ ጊዜ በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።

በዚሁ መሰረት፡

    ተጫራቾች በሥራ ዘርፉና ሌሎች ተያያዥ ሥራዎች የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (TIN) ማቅረብ የሚችሉ።

    ተጫራቾች ለጨረታው ውድድር ከሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ በየሎት 200,000 /ሁለት መቶ ሺህ/ ሲሆን የሎት ብዛት እና የእህሉ መጠን በሚሸጥ ሰነድ ላይ የሚገለጽ ይሆናል። የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተመሰከረለት የክፍያ ማዘዣ (CPO) ማቅረብ አለባቸው። የጨረታው ሰነድ ይህ ጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 10ኛው ቀን ድረስ የማይመለስ ብር 400 በመክፈል በሀዋሳ ከተማ በድርጅቱ የግዥ ፋይ/ንብ/አስ/ክፍል ቢሮ ቁጥር 12 መግዛት ይችላሉ።

    ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነድ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10 ቀናት ውስጥ በሰም በታሸገ ፖስታ/ኤንቨሎፕ በማድረግ ኦሪጂናልና ኮፒውን ለየብቻው ከተጓዳኝ ማስረጃዎች ጋር በማደራጀት በድርጅቱ የግዥ ፋይ//አስ/ክፍል ቢሮ ቁጥር 12 ለዚሁ ጨረታ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ 10ኛው ቀን እስከ 800 ሰዓት ማስገባት አለባቸው።

    የጨረታው ሳጥን የጨረታው ማስታወቂያ በወጣ 10ኛው ቀን ከቀኑ 800 ሰዓት ታሽጐ በእለቱ 830 ሰዓት በድርጅቱ ግዥ ፋይ/ንብ/አስ/ክፍል ቢሮ ቁጥር 12 ተጫራቾች ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። ነገር ግን 10ኛው ቀን የሥራ ቀን ባይሆን በቀጣዩ የሥራ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ተመሳሳይ ቦታ ሰዓትና ሁኔታ ይከፈታል።

    ድርጅቱ ለዚሁ ጨረታ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

በስልክ ቁጥር 046 220 1752/2285/2117

 

የደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት

 

Save Tender