የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ከዚህ በታች የተጠቀሱትን አቅርቦቶች ፍላጎት ካላቸው የአገር ውስጥ ድርጅቶች አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል.
የጨረታ ማስታወቂያ
ERC DSPA ግ.ጨ.ቁ 14/2018
የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ከዚህ በታች የተጠቀሱትን አቅርቦቶች ፍላጎት ካላቸው የአገር ውስጥ ድርጅቶች አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል.
- የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ ( Electric Vehicle) ግዢ
በመሆኑም በጨረታው መሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች የሚከተሉትን ህጋዊ ሰነዶች ማሟላት አለበት፡-
- የታደሰ ንግድ ፍቃድ
- የተጨማሪ እሴት ታክስ
- በዘርፉ የአቅራቢነት ምዝገባ ሰርተፍኬት
- የግብር ከፋይ ምዝገባ ሰርተፍኬት /ቲን/
- ታክስ ክሊራንስ
- ተጫራቾች በሽርክና በጥምረት በጋራ ወይም በቅንጅት የሚጫረቱ ከሆነ የመመስረቻ ሰነድ ማቅረብ አለባቸው፤
- ርክክቡ የሚፈጸምበት ቦታ የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋናው መስራያ ቤት ነው፤
- ጨረታው ፀንቶ የሚቆየው ለ 30 (ሰላሳ) ቀናት
- የጨረታ ማስከበሪያ መጠን
- ሎት- 1 ( Light Electric Vehicle 1 ) 120,000.00 / መቶ ሀያ ሺ/ ብር ሆኖ የጨረታ ማስከበሪያው በሲ.ፒ.ኦ ፤ በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ሆኖ ጨረታ ከተከፈተበት 60 (ስልሳ) ቀናት የሚቆይ መሆን ይኖርበታል
- ሎት- 2 ( Light Electric Vehicle 2 ) የጨረታ ማስከበሪያ መጠን 520,000.00 /አምስት መቶ ሺ/ ብር ሆኖ የጨረታ ማስከበሪያው በሲ.ፒ.ኦ ፤ በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ሆኖ ጨረታ ከተከፈተበት 60 (ስልሳ) ቀናት የሚቆይ መሆን ይኖርበታል
- ሰነድ ለመግዛት የምትፈልጉ ተጫራቾች ሰነዱ በሚገኝበት የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና መ/ቤት በፋይናስ ክፍል ቢሮ ቁጥር 73 የማይመለስ 500./አምስት መቶ ብር/ በመክፈል መውሰድ ትችላላችሁ፡፡
- ጨረታው አየር ላይ የሚውልበት ቀን 12/09/2018 ዓ.ም ፤
- ጨረታው የሚዘጋው፡-25/09/2018 ዓ.ም ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ሆኖ በእለቱ ከሰዓት 9፡30 ይከፈታል፡፡
- የሚቀርበው እቃ አይነትና ይዘት በጨረታ ሰነዱ የተገለጹ መስፈርቶችን አሟልቶ መቅረብ የሚችል ፤
- ኮርፖሬሽኑ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው
- ለበለጠ መረጃ እና ማብራሪያ ዋናው መስሪያ ቤት በሚገኝበት አዲስ አበባ መሻለኪያ ከሸዋ ዳቦ ፊት ለፊት የቀድሞው አራተኛ ክፍለ ጦር ግቢ በአካል ወይም በስልክ 0114702063/0114702064 መጠየቅ ይቻላል፡፡
የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን
አዲስ አበባ
