Tender Detail

Tender Details

  • Company Catholic Caritas Ethiopian
  • Address , Phone:
  • Website
  • Deadline05 Jun 2026, 9:30 AM
  • magazineReporter Tenders
  • Bid Document Price
  • opening date2026-06-05 10:00:00
  • Categories

ካቶሊክ ካሪታስ ኢትዮጵያ መሰረቱን በኢትዮጵያ ያደረገ በጎ አድራጎት ድርጅት በሶዶ /ጽ/ቤት Agriculture-focused Dignified Employment for Youth ADEY በተሰኘ ፕሮጀክት ከ Master Card Foundation  በATI  በኩል በተገኘው የገንዘብ ድጋፍ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አበላ አባያ (ወላይታ ዞን) ፣ ዳራማሎ (ጋሞ ዞን) ፣ ዴራሼ (ዳርዱላ) እና ኮልሜ (ኮንሶ ዞን) ወረዳዎች ለስራ-አጥ ወጣቶች ለእርባታ እና ለማሞከት የሚሆኑ የአከባቢ/የተዳቀሉ በጎችንና ፍየሎችን በህጋዊ ጨረታ አወዳድደሮ ገዝቶ ለማሰራጨት ይፈልጋል፡፡


የጨረታ ማስታወቅያ

ካቶሊክ ካሪታስ ኢትዮጵያ መሰረቱን በኢትዮጵያ ያደረገ በጎ አድራጎት ድርጅት በሶዶ /ጽ/ቤት Agriculture-focused Dignified Employment for Youth ADEY በተሰኘ ፕሮጀክት ከ Master Card Foundation  በATI  በኩል በተገኘው የገንዘብ ድጋፍ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አበላ አባያ (ወላይታ ዞን) ፣ ዳራማሎ (ጋሞ ዞን) ፣ ዴራሼ (ዳርዱላ) እና ኮልሜ (ኮንሶ ዞን) ወረዳዎች ለስራ-አጥ ወጣቶች ለእርባታ እና ለማሞከት የሚሆኑ የአከባቢ/የተዳቀሉ በጎችንና ፍየሎችን በህጋዊ ጨረታ አወዳድደሮ ገዝቶ ለማሰራጨት ይፈልጋል፡፡

በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘሩት መሥፈርቶችን፡-

  1. በዘርፉ ለአመቱ የታደሰ የንግድ ፍቃድ
  2. የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ
  3. የታክስ ከፋይነት ምዝገባ የምስክር ወረቀቶች ቅጂዎችን
  4. ቀደም ስል ተመሳሳይ ሥራ የሠሩበት የስራ ልምድ ማስረጃ ወይም የካምፓኒ ፕሮፋይል ማቅረብ
  5. ካሸነፉበት ወረዳ የአከባቢ/የተዳቀሉ በጎችንና ፍየሎችን በተቀመጠዉ መስፈርት መሰረት ገዝቶ ለማቅረብ ፈቃደኛ የሆኑ ተጫራቾች መወዳደር የሚትችሉ መሆኑን እየገለጽን
  6. ጨረታው ክፍት በሆነ አሰራር ይፈፀማል
  7. ዝርዝር መረጃ የያዘውን መወዳደሪያ ሰነድ ተጫራቾች ጨረታው ከወጣበት ቀን ግንቦት 17/2018 ዓ.ም እስከ ግንቦት 28/2018 ዓ.ም ዘወትር በሥራ ሰዓት በካቶሊክ ካሪታስ ኢትዮጵያ በሶዶ ጽ/ቤት የብሮ ቁጥር G4 የማይመለስ ብር 500 /አምስት መቶ/ በድርጅቱ ስም በኢት/ያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000018269221 ­­­­(ECS SDCO SEVERANCE FUND) በማስገባትና የከፈሉበትን የባንክ ገቢ ደረሰኝ በማምጣት ካቶሊክ ካሪታስ ኢትዮጵያ ሶዶ ጽ/ቤት በአካል በመገኘት መግዛት ይችላሉ፡፡
  8. ሁሉም ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ከጠቅላላው የጨረታ መጠን 2% የጨረታ ማስከበርያ ስፒኦ (CPO) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  9. ሁሉም ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ ምልክት የተደረገበት አንድ “ኦሪጅናል” እና አንድ ቅጂ ልክ እንደ መጀመሪያዉ በተመሳሳይ መልኩ የተፈረመ እና ርዕሱን በመግለጽ “ኮፒ” የሚል ምልክት የተደረገበት በሴም የታሸገ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  10. ጨረታው ይህ ማስታወቅያ በጋዜጣ ከወጣበት በ10ኛው የስራ ቀን ማለትም ግንቦት 28/2018 ዓ.ም ከቀኑ 9፡30 እስከ 10፡00 ሰዓት ገብቶ በተመሳሳይ ቀን ከሰዓት በኋላ 10፡00 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወክሎቻቸው በተገኙበትም ሆነ ባልተገኙበት ካቶሊክ ካሪታስ ኢትዮጵያ በሶዶ ጽ/ቤት ቢሮ ይከፈታል፡፡
  11. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፍል ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠራዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

አድራሻ:-  ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ወላይታ ዞን፣ ሶዶ ከተማ፣ድል በትግል ቀበሌ፣

Email ፡- eccscs2020@gmail.com

Save Tender