የጽህፈት መሳሪያዎች፣ የጽዳት እቃዎች፣ የኤሌክትሮኒክስ እና የፈርኒቸር እቃዎች ግዢ የጨረታ ማስታወቂያ
በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን የወንዶ ገነት ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ እና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት በ2019 ዓ.ም በጀት ዓመት ለሴከተር መ/ቤቶች ከዚህ በታች የተጠቀሱትን የቢሮ እቃዎችን በጨረታ እወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
1. ሎት -1 የጽህፈት መሳሪያ
2. ሎት 2 የጽዳት እቃዎች
3. ሎት-3 የኤሌከትሮኒክስ እቃዎች
4. ሎት-4 የፈርኒቸር እቃዎች
በጨረታው ላይ ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች :-
1. የታደሰ የዘርፉ ንግድ ስራ ፍቃድ፣ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣ ቫት ተመዝጋቢ የሆኑ እና የአቅራቢነት ምዝገባ ምስከር ወረቀት ያላቸው፡፡
2. የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ በባንክ የተረጋገጠ ብር 20,000 (ሃያ ሺህ ብር) ለብቻ ከግዴታ ሰነዶች ጋርአሽገው ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
3. የጨረታ ሰነዱን በተጫራቾች መመሪያ መሠረት ተሞልቶ የእቃዎቹን ዋጋ መሙያ ሰነድ ፋይናንሽያል አንድ ኦርጅናል እና ሁለት ኮፒ ለብቻው በማሸግ እና እንዲሁም የግዴታ ሰነዶችን ከጨረታ ማስከበሪያው ጋር ለብቻው በአንድ ፖስታ ውስጥ በማድረግ በሁሉም ዶከመንት ላይ ህጋዊ የሆነ የድርጅቱን ማህተብ በማሳረፍ እና አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን በመሙላት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይየስራ ቀናት በየሎቱ የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) በወንዶ ገነት ከተማ ገቢዎች ቅ/ጽ/ቤት ከፍለው የከፈሉትን ደረሰኝ በማሳየት የጨረታ ዶከመንቱን ከወንዶ ገነት ከተማ ፋ/ኢ/ል/ጽ/ቤት መውሰድ ይችላል፡፡
4. የጨረታው ሳጥኑ ጋዜጣው አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጨምሮ ለı5 ተከታታይ ቀናት የስራ ቀናት እስከ መጨረሻው ቀን 11 ፡30 ድረስ ሲሸጥ ይቆይ እና በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ላይ ታሽጎ በ4፡30 ሰዓት ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ይከፈታል፡፡
5. በጨረታው ሰነዱ ላይ ስርዝ ድልዝ ወይም ለመለየት አሻሚ ነገር መኖር የለበትም፡፡ ካለም ተጫራቹ ፓራፍ ማድረግ አለበት፡፡
6. የወቅቱን ዋጋ ያላገናዘበ የጨረታ ዋጋ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ ከቀረቡም የወቅቱን ዋጋ ትንታኔ እንዲያቀርቡ ይደረጋል፡፡
7. አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉባቸው እቃዎች እስከ ወንዶ ገነት ከተማ አስተዳደር ፋ/ኢ/ል/ጽ/ቤት ድረስ በራሳቸው ወጪ አጓጉዞ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
8. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ በጨረታው አይገደድም፡፡
ማሳሰቢያ፡- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡ በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን የወንዶ ገነት ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ እና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት
ለበለጠ መረጃ
ስልክ ቁጥር 0916134401/ 0916046074 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን የወንዶ ገነት ከተማ አስተዳደርፋይናንስ እና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት
