Tender Detail

Tender Details

  • Company በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የአዳሚ ቱሉ የፀረ-ተባይ ማዘጋጃ ፋብሪካ
  • Address አዳሚ ቱሉ እና አዲስ አበባ አዳሚ ቱሉ ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 011 662 4656
  • Website
  • Deadline28 Feb 2024, 12:11 AM
  • magazine
  • Bid Document Price
  • opening date
  • Categories Organizational

በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ


በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የአዳሚ ቱሉ የፀረ-ተባይ ማዘጋጃ ፋብሪካ የሚያመርታቸውን ምርቶች ተደራሸነቱን በሁሉም ከልሎች ለማስፋፋት ተጨማሪ የምርት ወኪል አከፋፋይ ድርጅቶችን በጨረታ ቁጥር APPF/SP/03/16 አወዳድሮ ከአሸናፊዎች ጋር ውል በመፈራረም አብሮ መስራት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ለወኪል አከፋፋይነት በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩ

መስፈርቶችን በሟሟላት መወዳደር ይችላሉ፡፡

1) ተጫራቾች በፀረ-ተባይ ንግድ የተሰማሩ እና ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆናቸውን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸው::

2) ተጫራቾች ስለ ጨረታው ዝርዝር ሁኔታ የሚገልፀውን ሰነድና መመሪያ አዳሚ ቱሉ ባለው የፋብሪከው ዋና መሥሪያ ቤት ንግድ መምሪያ ቢሮ ወይም አዲስ አበባ ቦሌ ሩዋንዳ ጂቡቲ ኤምባሲ ፊትለፊት ከሚገኘው ማስተባበሪያ ቢሮ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ዘወትር በሥራ ቀናት ከጠዋቱ 200 እስከ 600 ሰዓት እና ከሰዓት እስከ 1000 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ መግዛት ይችላሉ::

3. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 250,000.00 (ሁለት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር) በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የአዳሚ ቱሉ የፀረ-ተባይ ማዘጋጃ ፋብሪካ ስም በማዘጋጀት በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ዋስትና ወይም በኢንሹራንስ ዋስትና ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

4. ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዶች በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ለጨረታው የተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ከጨረታው መዝጊያ ሰዓት በፊት ማስገባት ይጠበቅባቸዋል፡፡

5. ጨረታው የካቲት 28 ቀን 2016 . ጠዋት 400 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 430 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት አዲስ አበባ ቦሌ ሩዋንዳ ጂቡቲ ኤምባሲ ፊትለፊት በሚገኘው ማስተባበሪያ ቢሮ የሚከፈት ይሆናል፡፡ የተጫራቾች በጨረታ መከፈቻ ቀንና ሰዓት ያለመገኘት የጨረታውን ሂደት አያስተጓጎልም፡፡

6. የጨረታ ሳጥኑ ከተዘጋ በኋላ የሚቀርብ የጨረታ መወዳደሪያ ሰነድ ተቀባይነት የለውም፡፡

7. ፋብሪካው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡

ለበለጠ  መረጃ፡ . ማስተባበሪያ ስልክ ቁጥር 011 662 4656 / 0464419164 (ማዞሪያ): 0991589980 (ንግድ መምሪያ ፓ.ሣ.ቁ 1206 (አ.አ) 247 (አ/ቱሉ)

በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን አዳሚቱ

 የፀረ-ተባይ ማዘጋጃ ፋብሪካ

Save Tender