የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት የተለያዩ የሥራ አልባሳት፥የድርጅቱ ዓርማ የሚታተምበት መለዮና ከረባት፥የተለያዩ ጫማዎች (የሥራና የሴፍቲ ጫማዎች)በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር 01/2019
የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የሥራ ትጥቆች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ምድብ 1 የተለያዩ የሥራ አልባሳት
ምድብ 2 የድርጅቱ ዓርማ የሚታተምበት መለዮና ከረባት
ምድብ3. የተለያዩ ጫማዎች (የሥራና የሴፍቲ ጫማዎች)
ስለሆነም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መመዘኛዎች ማሟላት የሚችሉ ድርጅቶች መወዳደር ይችላሉ።
1. በጨረታው ለመካፈል በዘርፉ ህጋዊ የሆነ የንግድ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ የግብር ከፋይነት ሰርተፊኬት (TIN No.) ያላቸው፡፡
2. የገንዘብ ሚኒስቴር ባወጣው የአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስከር ወረቀትና ጨረታ ላይ እንዲሳተፉ ከሀገር ውስጥ ገቢ መ/ቤት የሚሰጣቸውን የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
3. በተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ግብር ከፋይነት የተመዘገቡና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
4. ተጫራቾች ለምድብ 1፡ ብር 150,000.00 (አንድ መቶ ሃምሳ ሺህ ብር)፣ ለምድብ 2፡ ብር20,000.00 (ሃያ ሺህ ብር )፣ እና ለምድብ 3፡ ብር 60,000.00 (ስልሳ ሺህ ብር) የጨረታ ማስከበሪ ዋስትና ( Bid Bond ) ወይም በባንክ በተረጋገጠ ቼክ (CPO) ከጨረታ ሰነዱ ጋርአያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
5. ተጫራች የመወዳደሪያ ሰነድ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ እስከ 25/12/2018 ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ድረስ በድርጅቱ የስብሰባ አዳራሽ ቢሮ ቁጥር 602 ለዚህ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
6. ጨረታው በዚሁ ቀን 25/02/2018 ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚያው ዕለት 4:05 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት በቢሮ ቁጥር 602 ይከፈታል፡፡
7. ተጫራቾች ለእያንዳንዱ ምድብ የጨረታውን ሰነድ የማይመለስ ብር 300.00 (ሦስት መቶ ብር) በመከፈል ይህ ጨረታ ከወጣበት ቀን አንስቶ ከድርጅቱ ግዥና ትራንስፖርት ከፍል ቢሮ ቁጥር11 መውሰድ ይችላሉ፡፡
8. ተጫራቾች ለሶስቱም ምድብ ናሙና የማቅረብ ግዴታ አለባቸው::
9. ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
አድራሻ፡- ሜክሲኮ አደባባይ ወደ ሳርቤት በሚወስደው መንገድ 300 ሜትር ዝቅ ብሱ
የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት
ስልክ ቁጥር 0115525405/011-551-32 88
የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት
