አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ. ቶዮታ ደብል ጋቢና እና የጭነት ተሽከርካሪ በግልፅ ሐራጅ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል
ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ የሐራጅ ማስታወቂያ
አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ. በአዋጅ ቁጥር 97/1990 እና 216/1992 እንዲሁም በአዋጅ ቁጥር 1147/2011በተሰጠው ስልጣን መሰረት በሰንጠረዡ ላይ የተዘረዘሩትን ንብረቶች በግልፅ ሐራጅ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
|
ተ.ቁ |
የተበዳሪ ስም |
የአስያዥ ስም |
አበዳሪ ቅርንጫፍ |
የመኪናዉ ዓይነት፤ የሰሌዳ ቁጥር፣ የሻንሲ ቁጥርና የሞተር ቁጥር |
የመነሻ ዋጋ
|
የጨረታ ቀን
|
||||
|
የሰሌዳ ቁጥር |
የመኪና ዓይነት |
የሞተር ቁጥር |
የሻንሲ ቁጥር |
የስሪት ዘመን |
||||||
|
1 |
አቶ ያሬድ ተ/መድህን መንግስቱ |
አቶ ያሬድ ተ/መድህን መንግስቱ |
ቦሌ
|
አአ-03-64338 |
ቶዮታ ደብል ጋቢና |
2KD-5037359
|
MROFR22 G3A0566677 |
2010 |
4,000,000
|
ነሐሴ 14 ቀን 2016ጠዋት 4፡00-6:00 |
|
2 |
ኢት-03-41940 |
የጭነት ተሽከርካሪ
|
B219-159526
|
WJME3T R540 C231637 |
2010 |
5,000,000 |
ነሐሴ 15 ቀን 2016ጠዋት 4፡00-6:00 |
|||
ማሳሰቢያ
- ተጫራቾች የጨረታ መነሻ ዋጋ አንድ አራተኛ (1/4ኛ) ወይም 25% በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ሰነድ (CPO) ብቻ በአንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ አማ ስም በማሰራትና ለጨረታ ማስከበሪያነት በማስያዝ መጫረት ይችላሉ።
- ጨረታው የሚካሄድበት ቦታ በተመለከተ በሰንጠረዡ የተገለጹት ንብረቶች ጨረታ የሚሄደው 22 አካባቢ በሌክስ ፕላዛ ሕንፃ ላይ በሚገኘው የባንኩ ዋና መስሪያ ቤት የስብሰባ አዳራሽ ይሆናል።
- የተጫራቾች ምዝገባ የሚከናወነው ከ4፡00 - 5:30 ድረስ ይሆናል። ምዝገባው ከተጠናቀቀ በኋላ ለንብረቱ የሚመደበው የጥሪ ሰዓት 30 ደቂቃ ብቻ ሲሆን የጨረታው መጠናቀቂያ ሰዓት ድረስ አሸናፊው ካልተለየ አሸናፊ እስኪለይ ድረስ ጨረታው የሚቀጥል ይሆናል።
- በጨረታው የተሻለ ዋጋ ያቀረበ ተጫራች ጨረታውን ከሚያካሂደው የባንኩ የህግ አገልግሎት መምሪያ ማሸነፉን የሚገልጽ ደብዳቤ ሲደርሰው ብቻ አሸናፊ ይባላል።
- የጨረታው አሸናፊ ቀሪውን ገንዘብ አሸናፊነቱ በደብዳቤ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ በአስራ አምስት (15) ቀናት ውስጥ አጠቃሎ መክፈል ይኖርበታል። በእነዚህ ቀናት ውስጥ ካልከፈለ የሐራጁ ውጤት ተሰርዞ ለጨረታ ማስከበሪያ በሲ.ፒ.ኦ (CPO) ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል፡፡ በጨረታው የተሸነፉ ተጫራቾች ያስያዙት ገንዘብ ይመለስላቸዋል።
- የጨረታው አሸናፊ ካሸነፈበት ዋጋ ላይ 15% (አስራ አምስት በመቶ) ተጨማሪ እሴት ታክስ ጨምሮ ይከፍላል።
- ባንኩ ለአሸናፊ ተጫራች ከሚገዙበት ዋጋ ከ ሃምሳ በመቶ (50%) ያልበለጠ የብድር አገልግሎት ሊያመቻች ይችላል።
- ለጨረታ የቀረቡትን ንብረቶች ለመጎብኘት የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች የጨረታው ቀን ከመድረሱ ከ7 (ሰባት) የስራ ቀናት አስቀድሞ ከባንኩ ጋር ቀጠሮ በማስያዝ መጎብኘት ይችላል።
- በሐራጅ ጨረታው ላይ መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች፣ ተበዳሪዎች እና ንብረት አስያዥ ወይም የነዚህ ሕጋዊ ተወካዮች ብቻ ናቸው። ተበዳሪዎች እና ንብረት አስያዦች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው የጨረታዉን ሂደት ለመከታተል በተጠቀሰዉ ቦታ እና ሰዓት እንድትገኙ እያሳሰብን ካልተገኛችሁ በሌላችሁበት ጨረታው የሚከናወን መሆኑን እንገልፃለን።
- ባንካችን ንብረቱ በገዢው ስም እንዲዞር ለሚመለከተው መንግስታዊ አካል ደብዳቤ ይፅፋል።
- ከሚሸጠው ንብረት ጋር የተያያዙ ማንኛውም ለመንግስት ሊከፈል የሚገቡ ክፍያዎች፣ ወጪዎች ወይም ግብር እንዲሁም በንብረት ማስተላለፍ ሂደት የሚመጡ ማንኛውም አይነት ክፍያዎች ወይም ግብር ሙሉ በሙሉ የጨረታ አሸናፊው/ገዥው/ የሚሸፍን ይሆናል።
- ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ለበለጠ ማብራርያ ወይም የጉብኝት ቀጠሮ ለማመቻቸት አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ ዋና መ/ቤት ሕግ አገልግሎት መምሪያ በስልክ ቁጥር 011-662-7120 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ.
