ናሽናል ሲሚንቶ አ.ማ. UPS 15KVA ከአቅራቢዎች አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
ናሽናል ሲሚንቶ አ.ማ. UPS 15KVA ከአቅራቢዎች አወዳድሮ ለመግዛት ጨረታ ያወጣ ሲሆን
ተጫራቾች
- በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው፤ የዘመኑን ግብር የከፈሉና ቫት ተመዝጋቢ ለመሆናቸው የማይመለስ ፎቶ ኮፒ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ይህ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ላሉት 3 ወራት ህጋዊ ሆኖ የሚቆይ የጨረታ ማስከበሪያ ሲ.ፒ.ኦ. 50,000.00 (ሀምሳ ሺህ) ብር ማስያዝ አለባቸው፡፡
- የጨረታው ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ ባሉት ቀናት እስከ ሐምሌ 24/2016 ዓ.ም ክፍት ሆኖ የሚቆይ ሲሆን ሐምሌ 24/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ጨረታው ተዘግቶ ሐምሌ 29/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ በሚገኘው ናሽናል ሲሚንቶ ኢማ ከጠዋቱ 4፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች ከላይ በተገለጸው መስፈርት መሰረት የአንዱን UPS 15KVA ዋጋ በግልጽ በማስቀመጥ ሳር ቤት ግደይ ገ/ህይወት ህንጻ 3ኛ ፎቅ አ.አ. ስልክ፡ 25 1114 42 19 28/0960-36-71-36 ግዢ ክፍል እና ድሬዳዋ ናሽናል ሲሚንቶ ኢማ ስልክ ቁጥር 0935- 98-50-53/0946-43 93 94 ግዢ ክፍል በ ፖስታ ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ፡፡
- ጨረታ ሳጥኑ ከተዘጋ በኋላ የሚመጣ የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት የለውም፡፡
ማሳሰቢያ፡-
- ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም ጨረታው ተከፍቶ ውሳኔ ይሰጥበታል፡፡ መ/ቤቱም የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብት አለው።
ናሽናል ሲሚንቶ አ/ማ
