የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ በ2017 በጀት ዓመት Video Camera & Accessories ፣ ዲጂታል መታወቂያና ባጅ ማተሚያ ማሽን ፣ C-Band 5G LNB & Band Pass Filter ፣ መኪና ላይ የሚገጠም GPS ፣ Portable LED Video Wall Screen ግዥ መፈጸም ይፈልጋል
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ በ2017 በጀት ዓመት የሚገለገልባቸውን እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
በዚህም መሠረት –
- ሎት 1. Video camera & Accessories ግዥ
- ሎት 2, ዲጂታል መታወቂያና ባጅ ማተሚያ ማሽን ግዥ
- ሎት 3. C-Band 5G LNB & Band pass Filter ግዥ
- ሎት 4. መኪና ላይ የሚገጠም GPS ግዥ
- ሎት 5. Portable LED video Wal Screen ግዥ
በጨረታ ቁጥር ኢ.ሚ.ኔ.ብ.ግ.ጨ.001/2017 በግልጽ ጨረታ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለመግዛት የሚፈልግ በመሆኑ በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ -
- በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉና የገቢዎች ከሊራንስ ያላቸው፡፡
- የተጨማሪ እሴት ታክስ እና የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር የምዝገባ ሰርትፍኬት ማቅረብ የሚችሉና፡በግዥ አቅራቢነት የተመዘገቡ፡፡
- ተጫራቾች በሚያቀርቡት እያንዳንዱ ሰነድ እና ፖስታ ላይ የድርጅቱን ማህተምና ፊርማቸውን ማኖር ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ለሚያቀርቡት አጠቃላይ ዋጋ ለእያንዳንዱ
- ለሎት 1 የጨረታ ማስከበሪያ ብር 500,000.00 ፣
- ለሎት 2 የጨረታ ማስከበሪያ ብር 500,000.00
- ለሎት 3 የጨረታ ማስከበሪያ ብር 50,000.00
- ለሎት 4 የጨረታ ማስከበሪያ ብር 50,000.00
- ለሎት 5 የጨረታ ማስከበሪያ ብር 50,000.00 በባንክ በተረጋገጥ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
5. ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር የሚያሳይ የጨረታ ሰነድ ይህ ማስታወቂ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከሎት 1- 5 ላሉት ጨረታዎች 10 የስራ ቀናት ውስጥ አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ቢሮ ቁጥር 28 የማይመለስ ብር ለእያንዳንዱ 300.00 /ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል ዘወትር በሥራ ሰዓት መግዛት ይችላሉ፡፡
6. ጨረታው በ11ኛው ቀን ከቀኑ 4፡00 ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከቀኑ 4፡30 ተጫራቾች /ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 34 ይከፈታል፡፡ ሆኖም ግን የተጫራቾች አለመገኘት ጨረታውን ከመክፈት አያግደውም፡፡ የመክፈቻው ዕለት በዓል/እረፍት ቀን ከሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ተዘግቶ ይከፈታል፡፡
7. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሃሳባቸውን ዋናውንና ኮፒውን / ቴክኒካል ኦሪጅናልና ኮፒ፣ ፋይናንሽል ኦሪጂናልና ኮፒ በተለያየ ፖስታ በማሸግ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል፡፡
8. በአንዱ ተጫራች ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ የተከለከለ ነው፡
9. በጨረታ ያሸነፈ ተጫራች ከመ/ቤታችን ጋር ጨረታውን እንዳሸነፈ ካወቀበት ጊዜ አንስቶ በ15 ቀናት ውስጥ በሲፒኦ የጠቅላላ ዋጋውን 10% በማስያዝ ውል መዋዋል ይኖርበታል፡፡
10. ተቋሙ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ
የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ 5 ኪሎ ቅድስት ማሪያም ቤ/ክርስቲያን ከማህበረ ቅዱሳን ጀረባ ያለው ህንፃ ፡፡
ለበለጠ መረጃ ስልክ 011 111 16382 መደወል ይችላሉ፡፡
የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ
